በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ማረሚያ ቤቶች አስ/ርኮሚሽን የስልጤ ዞን የወራቤ ማረሚያ ተቋም በ2018 በጀት ዓመት በህግ ጥላ ስር ለሚገኙ የህግ ታራሚዎች የምግብ እህሎች እና የማገዶ የባህር ዛፍ እንጨት በጨረታ አወደድሮ መግዛት ይፈልጋል
የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 02/2018
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ማረሚያ ቤቶች አስ/ርኮሚሽን የስልጤ ዞን የወራቤ ማረሚያ ተቋም በ2018 በጀት ዓመት በህግ ጥላ ስር ለሚገኙ የህግ ታራሚዎች ለምግብ አገልግሎት የሚሆን በሎት1 ቅጭቅጭ የወጣለት የተበጠረ ሰርገኛ ጤፍ፣በቆሎ፣ አተር፣ ፍርኖ ዱቄት፣ ባቄላ በሎት 2 አንበሳ ሻይ ቅጠል፣ጨው፣ስኳር፣ ዘይት በሎት 3 ጎመን ዘር፤የተፈጨ በርበሬ፣ ቅያ ሽንኩርት ነጭ ሹንኩርት፣ሞኮረኒ፣ፓስታ፣ሩዝ፣ ምስር ክክ፣አተር ክክ እና የተለያዩ ቅመማ ቅመም በሎት 4 የማገዶ የባህር ዛፍ እንጨት ከጥር 1/5/2018 ዓ/ም እስከ ሰኔ 30/10/2018 ዓ/ም በጨረታ አወደድሮ መግዛት ይፈልጋል።
በዚህም መሠረት፡-
- በዘርፉ ህጋዊ ፍቃድ ያላቸውና በአቅራቢያዎች ዝርዝር ውስጥ የተመደቡ።
- የዘመኑን የመንግስት ግብር የከፈሉና የንግድ ፍቃዳቸውን ያሳደሱ።
- ቫት/VAT) ተመዝገቢ የሆኑ።
- ጨረታው ፀንቶ የሚቆይበት ግዜ ለ60 ቀናት።
- አሸናፊው ማንኛውንም ወጪ በራሱ ሸፍኖ ዕቃዎችን ወራቤ ማረሚያ ተቋም ቅጥር ግቢ ማቅረብ የሚችል።
- የጨረታው ማስከበሪያ 5000 (አምስት ሺ ብር) በኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ እውቅና ያለው የፋይናስ ተቋም የተረጋገጠ ቼክ፣ሌተር ኦፍ ክሬዲት፣ሲፒኦ ማቅረብ የሚችሉ።
- በጨረታው አሸናፊ የሚሆኑ ታጫራቾች በአሸነፉባቸው ዕቃ አይነቶች 10% ማስያዝ የሚችል።
- ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተከታታይ ባሉት 15 ቀናት ውስጥ ለሚወዳደሩበት አቅርቦት በዘርፉ የማይመለስ ብር 150 (አንድ መቶ ሃምሳ ብር) በመክፈል የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ከግዥና ፋይናንስ ቢሮ መውሰድ ይችለሉ.
- ታጫራቾች የዋጋ ማቅረቢያቸውንና የመወዳደሪያ ሃሳበቸውን በስም በተሸገ ኢንቨሎፕ በማድረግ አንድ ኦርጅናል እና አንድ ፎቶ ኮፒ እስከ 15ኛው ቀን 11፡00 ሰዓት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
- ጨረታው ይህ ማስታወቂያ ከወጠበት ቀን ጀምሮ 15ኛው ቀን ከቀኑ በ11፡00 ሰዓት ታሽጎ በ16ኛው ቀን በ3፡00 ተጫረቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። 16ኛው ቀን የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ከጠዋቱ 3፡00 ታጫረቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተኙበት ይከፈታል።
- ተቋሙ የተሸለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0911804123 መጠየቅ ይችላሉ
የወራቤ ማረሚያ ተቋም
