የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሰራተኞች ካፌና ሬስቶራንት እና መዝናኛ ክበብ በውል ለሁለት ዓመት የሚቆይ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ነገሮች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሰራተኞች ካፌና ሬስቶራንት እና መዝናኛ ክበብ በውል ለሁለት ዓመት የሚቆይ፡
- ሎት 1፡- የተለያዩ አትክልትና ፍራፍሬ
- ሎት 2፡- የከብት ስጋ እና የበግ ስጋ
- ሎት 3፡- የዓሳ ስጋ
- ሎት 4፡- የዶሮ ሥጋ
- ሎት 5፡- ወተት፣ ቅቤ እና አይብ
- ሎት 6፡- የታሸጉ ምግቦች እና የምግብ ግብዓቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ስለሆነም በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች የሚከተሉትን ቅድመ-ሁኔታዎች ማሟልት ይጠበቅባቸዋል፡-
- በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፈቃድ፤ የቲን ቁጥር ሰርተፍኬት፤ በጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል ከግብር ሰብሳቢ መ/ቤት የሚሰጥ ጊዜው ያላለፈበት የድጋፍ ደብዳቤ (ታክስ ክሊራንስ)፤ ለ120 ቀናት የሚቆይ የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ ወይም የባንክ ዋስትና ለእያንዳንዱ ሎት ብር 5,000.00 (አምስት ሺህ ብር) ወይም ከጥቃቅን እና አነስተኛ የሚሰጥ ደብዳቤ ማቅረብ የሚችሉ።
- ተጫራቾች ይህ ጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር ብቻ) በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ከሰራተኞች ካፌና ሬስቶራንት ጽ/ቤት መውሰድ ይችላሉ።
- ተጫራቾች ዋጋ የሚያቀርቡበት በገዙት ሰነድ ለዋጋ መሙያ በተዘጋጀው ቅጽ ላይ ብቻ ነው
- ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ 15% ወይም 3% የተጨማሪ እሴት ታክስ /AI/ ያካተተ መሆን አለበት።
- ተጫራቾች ማንኛውንም ማብራሪያ መጠየቅ ከፈለጉ ከጨረታው መክፈቻ 10 (አሥር) ቀን በፊት በደብዳቤ ማቅረብ ይችላሉ።
- ጨረታው በማስታወቂያ ከተለጠፈበት ቀን ጀምሮ በ15ኛው ተከታታይ የሥራ ቀን ጥር 15/2018 ዓ.ም በ8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚያው ቀን በ8፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በሰራተኞች ካፌና ሬስቶራንት አዳራሽ ይከፈታል።
- የኢንስቲትዩቱ ካፌና ሬስቶራንት የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ፡-
በስልክ ቁጥር፡- 011-230-51-02/0911-01-24-32/0910-98-15-19 መደወል ይችላሉ።
አድራሻ፡- ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል አጠገብ
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሰራተኞች ካፌና ሬስቶራንት
