ተስፋ ብርሃን ህፃናትና ቤተሰብ ልማት ድርጅት ከ ቻየልድ ፈንድ ኢትዮጲያ ባገኘዉ የገንዘብ ድጋፍ ለቀይት ጤና ጣቢያ የሲቢሲ ማሽን መግዛት ስለፈለገ በዘርፉ ከተሰማሩ አቅራቢ ድርጅቶች /ነጋዴዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ የሲቢሲ ማሽን ግዥ ጨረታ ማስታወቂያ
ተስፋ ብርሃን ህፃናትና ቤተሰብ ልማት ድርጅት ከ ቻየልድ ፈንድ ኢትዮጲያ ባገኘዉ የገንዘብ ድጋፍ ለቀይት ጤና ጣቢያ የሲቢሲ ማሽን መግዛት ስለፈለገ በዘርፉ ከተሰማሩ አቅራቢ ድርጅቶች /ነጋዴዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
በመሆኑም በዘረፉ የተሰማራችሁና በጨረታዉ ለመሳተፍ የምትፈልጉ
- በበጀት አመቱ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ያላችሁ
- የተጨማሪ እሴት ታክስ እና ቲን ቁጥር ያላችሁ እንዲሁም የመልካም ስራ አፈጻጸም ማስረጃ ማቅረብ የምትችሉ ድርጅቶች /ነጋዴዎች
ይህ ማስታወቂያ በሪፖርተር ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 10 (አስር) ቀናት የጨረታ ሰነዱን በብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) ቀይት ከሚገኘዉ የድርጅቱ ዋና ጽ/ቤት በመግዛት ለዚሁ በተዘጋጀዉ የጨረታ ሳጥን ዉስጥ የጠቅላላ ዋጋዉን 1 ፐርሰንት ከባንክ ሲፒኦ ጋር በፖስታ በማሸግ ሣጥን ዉስጥ በማስገባት እንድትወዳደሩ እየጋበዝን ጨረታዉ በ 11 (በአስረ አንደኛዉ ሰአት) ቀን በ4፡00 ሰአት ተዘግቶ በዚሁ ቀን በ4፡30 ሰአት የሚከፈት መሆኑን እየገለጽን 11ኛዉ ቀን በካላንደር የሚዘጋ በዓል ወይም ቅዳሜ እና እሁድ ከሆነ በሚቀጥለዉ የስራ ቀን የሚከፈት መሆኑን እናሳዉቃለን።
ማሳሰቢያ - ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታዉን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ተስፋ ብርሃን ህፃናትና ቤተሰብ ልማት ድርጅት
ደ/ብርሀን ከተማ አስተዳደር
ጣይቱ ክፍለ ከተማ
ቀይት ቀበሌ
ለተጨማሪ መረጃ ስ.ቁ 011-656-02-49/0961-14-07-05
ኢሜል: procurement@tesfab.org
