የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን በ2018.ዓ.ም በጀት ዓመት የሚገለገልባቸውን እቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን በ2018.ዓ.ም በጀት ዓመት የሚገለገልባቸውን እቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ በዚህም መሠረት፡-
· ሎት 1. የኤቭንት ኦርጋነዝር የአገልግሎት ግዥ
· ሎት. 2. የካሜራና ተዛማጅ ዕቃዎች ግዥ
በጨረታ ቁጥር አ.አ.ቱ ኮ.ግ.ጨ.001/2018 በግልጽ ጨረታ ተጫራቾችን አወዳድሮ ለመግዛት የሚፈልግ በመሆኑ በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ፡-
1. በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉና የገቢዎች ክሊራንስ ያላቸው።
2. የተጨማሪ እሴት ታክስ እና የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር የምዝገባ ሰርትፍኬት ማቅረብ የሚችሉና፣ በግዥ አቅራቢነት የተመዘገቡ፡፡
3. ተጫራቾች በሚያቀርቡት እያንዳንዱ ሰነድ እና ፖስታ ላይ የድርጅቱን ማህተምና ፊርማቸውን ማኖር ይጠበቅባቸዋል፡፡ ተጫራቾች ለሚያቀርቡት አጠቃላይ ዋጋ ለሎት.1 የጨረታ ማስከበሪያ ብር 150,000.00፣ ለሎት. 2 የጨረታ ማስከበሪያ ብር 200,000.00 ፣ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡ ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር የሚያሳይ የጨረታ ሰነድ ይህ ማስታወቂ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ጨረታዎች 10 የሥራ ቀናት ውስጥ ጨረታዉ የሚከፈትበት ቦታው የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን
4. የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን 4 ኪሎ ንብ ባንክ 7 ፎቅ የግ/ን/አ/ጠአ/ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 707 ይከፈታል፡፡
5. ቢሮ ቁጥር 707 የማይመለስ ብር የእንዱ የሰነዱ መግዧ 300.00 /ሶስት መቶ ብር/ በመክፈል ዘወትር በሥራ ሰዓት መግዛት ይችላሉ፡፡
6. ጨረታው በ11ኛው ቀን ከቀኑ 4፡00 ተዘግቶ በዚሁ ቀን ከቀኑ 4፡30 ተጫራቾች/ ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት -የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን 7ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 707 ይከፈታል፡፡ ሆኖም ግን የተጫራቾች አለመገኘት ጨረታውን ከመክፈት አያገደውም፡፡ የመክፈቻው ዕለት በዓል/ዕረፍት ቀን ከሆነ በቀጣዩ የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ተዘግቶ ይከፈታል፡፡
7. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሃሳባቸውን ዋናውንና ኮፒውን / ቴክኒካል ኦሪጅናልና ኮፒ፣ ፋይናንሻል ኦሪጂናልና ኮፒ በተለያየ ፖስታ በማሸግ ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይጠበቅባቸዋል፡፡
8. በአንዱ ተጫራች ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ የተከለከለ ነው።
9. በጨረታ ያሸነፈ ተጫራቶች ከመ/ቤታችን ጋር ጨረታውን እንዳሸነፈ ካወቀበት ጊዜ አንስቶ በ15 ቀናት ውስጥ በሲፒኦ የጠቅላላ ዋጋውን 10% በማስያዝ ውል መዋዋል ይኖርበታል፡፡
10. ተቋሙ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ ቦታው፡- የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን 4 ኪሎ ንብ ባንክ 7 ፎቅ ህንፃ፡፡
ለበለጠ መረጃ ስልክ +251 0111-25-07-33 መደወል ይችላሉ::
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቱሪዝም ኮሚሽን
