ድርጅታችን ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ የካስፐርስኪ አንቲ-ቫይረስ ግዥ ለመፈጸም ስለሚፈልግ ፍላጎት ያላቸውን ተጫራቾች በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 006/2018 ዓ.ም
ድርጅታችን የካስፐርስኪ አንቲ-ቫይረስ ግዥ ለመፈጸም ስለሚፈልግ ፍላጎት ያላቸውን ተጫራቾች በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
በመሆኑም መወዳደር የምትፈልጉ ተጫራቾች፡-
1. የታደሰ ንግድ ፍቃድና የዘመኑን ግብር ለመክፈላችሁ መረጃ ማቅረብ ይኖርባችኋል፤
2. ቫትን አካቶ የማይመለስ ብር 500 /አምስት መቶ/ በመክፈል ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የጨረታ ሠነዱን መካኒሳ በሚገኘው ዋናው መ/ቤት ገንዘብ ቤት ቢሮ ቁጥር 004 በመቅረብ መግዛት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፤
3. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዶቻቸውን ቴክኒካል እና ፋይናንሻል ሰነድ “ኦሪጅናል” እና “ፎቶ ኮፒ” ለየብቻው በታሸገ ኤንቨሎፕ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፤
4. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የጠቅላላ ዋጋውን 2 በመቶ በሲፒኦ ለብቻው በኤንቨሎፕ በማሸግ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፤
5. ተጫራቾች የሚያስገቧቸውን ሠነዶች እስከ ጥር 20 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት መካኒሳ በሚገኘው ዋናው መ/ቤት ግዥ ቢሮ ቁጥር 503 ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ጨረታው በዚያው ዕለት ከጠዋቱ 4፡15 ሠዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፤
6. ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ
ፖ.ሣ.ቁ.፡ 3516፣ ስልክ፡ 011 369 0563 ፋክስ፡ 011 5 513299
ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ
