በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2018 በጀት አመት በመደበኛ በጀት በወረዳው ውስጥ ለሚገኙ ሴክተር መስሪያ ቤቶች የሚሆን ጄነሬተር እና የውሃ መስመር ማሳለፊያ የብረት ቱቦ በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ ሀገር አቀፍ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ መለያ ቁጥር GGWW/0005/2018
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2018 በጀት አመት በመደበኛ በጀት በወረዳው ውስጥ ለሚገኙ ሴክተር መስሪያ ቤቶች የሚሆን ጄነሬተር እና የውሃ መስመር ማሳለፊያ የብረት ቱቦ በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል። በመሆኑም ለግዢ የቀረቡ እቃዎችና የጨረታ ማስከበሪያ CPO
ሎት አንድ ፡ ለጀኔሬተር የጨረታ ማስከበሪያ 10,000 ብር
ሎት ሁለት : ለውሃ መስመር ማሳለፊያ የብረት ቱቦ የጨረታ ማስከበሪያ 15,000 ብር ስለሆነ
ተወዳዳሪዎች፡-
1. የዘመኑን ንግድ ፍቃድ ያሳደሱ የቫት እና የቲን ነምበር ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚገልጽ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
2. የአቅራቢነት የምስክር ወረቀት በአላይን /online/ ሲስተም የተመዘገበ መሆን አለበት።
3. በጨረታው ለመወዳደር የሚፈልጉ ተወዳዳሪዎች የሚገዙትን ጨረታ ሰነድ ጠቅሰው በማመልከቻ ሲጠይቁ ተወካዮች ከሆነ ከድርጀቱ ህጋዊ ውክልና ይዘው መምጣት አለባቸው።
4. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 10ኛው ተከታታይ ቀናት 6፡00 ሰዓት ድረስ የማይመለስ ብር 100 ብር /አንድ መቶ/ ብር በመክፈል የጨረታውን ሰነድ ከገ/ጉ/ወ/ወ/ፋይናንስ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 3 ድረስ በመቅረብ የጨረታውን ሰነድ መግዛት ይችላሉ።
5. ተጫራቾች የጨረታውን ቴክኒካልና ፋይናንሺያል ዶክመንት ሲያቀርቡ ሀ/ቴክኒካል ዶክመንት አንድ አርጅናልና ሁለት ፎቶ ኮፒ በማድረግ ቴክኒካል በሚል በመለየት እና ለ/ለፋይናንሻል ዶክመንት አንድ ኦርጅናልና ሁለት ፎቶ ኮፒውን ኮፒ በማድረግ ፋይናንሻል በሚል በመለየት በሰም በማሸግ ከላይ የተጠቀሱት የጨረታ ማስከበሪያ /ሲፒኦ/ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ከቴክኒካል ኦርጅናል ዶክመንቱ ጋር በማድረግ በሰም ሁሉንም በአንድ እናት ፖስታ በማድረግ ፋይናንሻል ዶክመንት በሚል በመለየት ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመንጋዜጣ እየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 /አስር/ ተከታታይ ቀናት እስከ 8፡00 ሰአት ከገ/ጉ/ወ/ወ ፋይናንስ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 3 ድረስ በመምጣት ለጨረታ አገልግሎት በተዘጋጀው ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
6. የጨረታው ማስከበሪያ ሲፒኦ በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ስም ማሰራት አለበት፡፡
7. የጨረታው ሰነድ በ10ኛው ተከታታይ ቀናት ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ይታሸጋል፡፡ ከቀኑ 8፡30 ደግሞ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
8. መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ማሳሰቢያ፡-
1. በግዢ ኤጀንሲ በዕቃ አቅርቦት ምክንያት ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ድርጅቶች መወዳደር አይችሉም።
2. የቫት 7.5 ለወረዳው ገቢ የሚቆርጥ
3. ተጫራቾች ተጫርተው ያሸነፉአቸው እቃዎች የጥራት ችግር ያለባቸው መሆናቸው በቴክኒክ ጥራት ኮሚቴ ከተረጋገጠ ተመላሽ መሆኑን
4. ተጫራቾች ተጫርተው ያሸነፏቸው ማንኛውም እታ የወረዳው ማዕከል ማለትም ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት መሀል አምባ ማቅረብ ያለባቸው ሲሆን የወረዳው ማእከል ርቀት ከአዲስ አበባ 116 ኪ.ሜ ነው።
5. ጨረታው የሚከፈትበት ቀን በአል ወይም ቅዳሜና እሁድ ከሆነ ወደሚቀጥለው የስራ ቀን ይዘዋወራል፡፡
ለበለጠ መረጃ 0113360631/ 0143360146
ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት
መ/አምባ
