አር ቲ ኤን ኢትዮጵያ ድርጅት ከዩኒሴፍ ጋር በአጋርነት የሚሠራ መንግስታዊ ያልሆነ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሲሆን በበጀት ዓመቱ ዕቅድ መሠረት በፕሮጀክቱ ላቀፋቸው ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች የተለያዩ ጓሮ አትክልት ዘር አይነት በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ለ2ኛ ጊዜ የወጣ ጨረታ
የጨረታ ማስታወቂያ
አር ቲ ኤን ኢትዮጵያ ድርጅት ከዩኒሴፍ ጋር በአጋርነት የሚሠራ መንግስታዊ ያልሆነ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሲሆን በበጀት ዓመቱ ዕቅድ መሠረት በፕሮጀክቱ ላቀፋቸው ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች የተለያዩ ጓሮ አትክልት ዘር አይነት በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ቢያንስ የሚከተሉትን ማሟላት ይኖርባቸዋል፡፡
1. በጓሮ አትክልት ዘር ንግድ ፍቃድ ያለው የዘመኑ የታደሰ የንግድና የዋና ምዝገባ ፈቃዳቸውን፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡበትን ሰርተፍኬት፣ በጨረታ እንድትሳተፉ ለዘመኑ በጀት ዓመት ብቻ የሚያገለግል የምስክር ወረቀት እና ቲን ሰርተፍኬት ፎቶ ኮፒውን በማያያዝ የማይመለስ ብር 500.00 /አምስት መቶ ብር/ በመክፈል የጨረታ ሰነዱን በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ ሰባት የሥራ ቀናት ውስጥ ዘወትር በሥራ ሰዓት ከ 2፡30- 6፡30 እና ከ7፡30-11:00 ሰዓት ከላይ የተዘረዘሩትን መረጃዎች ዋናውንና ፎቶ ኮፒውን በማያያዝ ዲላ በሚገኘው አር ቲ ኤን ኢትዮጵያ ጽ/ቤት ሂሣብ ክፍል በመምጣት መግዛት ይችላሉ፡፡
2. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ኦርጅናልና ፎቶ ኮፒውን በሰም በታሸገ ኢንሽሎፕ (ፖስታ) የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ የጠቅላላ ዋጋውን 2 በመቶ በአር ቲ ኤን ኢትዮጵያ ድርጅት ስም ተሰርቶ በአርጅናል የጨረታ ሰነድ ውስጥ በማያያዝ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
3. ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ከሰባተኛው /7ኛው/ ቀን በኋላ ባለው የሥራ ቀን ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 6፡00 ድረስ ለዚህ ጨረታው ተብሎ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ ጨረታው በዕለቱ ከሰዓት 8፡00 ሰዓት ዲላ አር ቲ ኤን ኢትዮጵያ ድርጅት አዳራሽ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
4. ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 046-331-00-49/046-331-31-45 ዘወትር በሥራ ሰዓት ደውሎ መጠየቅና መረዳት ይቻላል፡፡
አድራሻ:- አር ቲ ኤን ኢትዮጵያ ድርጅት ዲላ ከተማ ከዲላይት ኢንተርናሽናል ሆቴል 100 ሜትር ገባ ብሎ፡፡
ሪች ዘ ኒዲ ኢትዮጵያ
