በኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን-የግብርና ውጤቶች ሽያጭና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ዘርፍ በአዳማ ቅርንጫፍ የተለያዩ ዓይነትና ደረጃ ያላቸው የተፈጥሮ ሙጫ ምርቶች ባሉበት ሁኔታ በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
በድጋሚ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
የተለያዩ ዓይነትና ደረጃ ያላቸው የተፈጥሮ ሙጫ ምርቶች ሽያጭ ጨረታ የጨረታ ቁጥር ኢግስኮ-የግ/ው/ሽ/ሜ/አ/ዘ/ግጨ/ሸ03/2018
በኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን-የግብርና ውጤቶች ሽያጭና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ዘርፍ በአዳማ ቅርንጫፍ የተለያዩ ዓይነትና ደረጃ ያላቸው የተፈጥሮ ሙጫ ምርቶች ባሉበት ሁኔታ በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም በዘርፉ የተሰማራችሁና ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ሁሉ በጨረታ መሳተፍ ይችላል።
1. በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፍቃድ፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር፤ (ተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ የምስከርነት ወረቀት የንግድ ምዝገባ የምስክርነት ወረቀት፣ በጨረታ ለመሳተፍ የሚሰጥ የምስክርነት ወረቀት (ክሊራንስ) ኮፒ ማቅረብ የሚችል እና በመንግስት ግዥ መመሪያ መሰረት በመንግስት ግዥ አቅርቦት የተመዘገቡ መሆን አለበት።
2. ተጫራቾች ለጨረታ ዋስትና የጨረታ ማስከበሪያ የጠቅላላ ዋጋውን ከ2% ያላነሰ በባንክ የተመሰከረ CPO በኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽ የግብርና ውጤቶች ሽያጭና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ዘርፍ ስም ከሚያቀርቡት የጨረታ ሰነዶች ጋር በማሸግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ የጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ ለ30 ቀናት የፀና መሆን ይኖርበታል፡፡
3. ማንኛውም ተጫራች የዋጋ ማቅረቢያ ቅጽ የሚጠይቀውን በሙሉ አሟልቶ ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡ የዕጣን ምርቶች ሽያጭ ተጫራቹ በሚሰጠው ዋጋ ላይ 15% ተጨማሪ እሴት ታክስ ይጨመራል።
4. ብቁ ተጫራቾች በአማርኛ ቋንቋ የተዘጋጀውን የተሟላ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 500.00 (ብር አምስት መቶ) በመክፈል ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጨረታው መክፈቻ ቀን ድረስ ዘወትር በሥራ ሰዓት (ከሰኞ እስከ ሀሙስ ከሰዓት በፊት ከ2፡00-6፡00፤ ከሰዓት በኋላ ከ7፡00-10:30 እንዲሁም ዓርብ፤ ከሰዓት በፊት ከ2:00-5:30 ከሰዓት በኋላ ከ7:30-10:30 በዘርፍ ጽ/ቤት ቃሊቲ ጉምሩክ ፊት ለፊት በኢግሥኮ-ግብርና ውጤቶች ሽያጭና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ዘርፍ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 206 እንዲሁም በአዳማ ከተማ መብራት ኃይል ንግድ ምከር ቤት ጎን አዳማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 2 በመቅረብ መግዛት ይችላሉ።
5. ጨረታው የካቲት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ከሰዓት 8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን የካቲት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ከሰዓት 8:30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸ በተገኙበት በዘርፉ 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 110 ይከፈታል፡፡
6. ተጫራቾች በጨረታ ሰነዱ ላይ ከቀረበው ዝርዝር ምርቶች ውስጥ በሙሉ ወይም በከፊል መጫረት ይቻላል፡፡
7. ማንኛውም ተጫራች በሌላ ተጫራች ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ አይችልም፤
8. ዘርፉ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉም ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
የግብርና ውጤቶች ሽያጭና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ዘርፍ
አዲስ አበባ 0114-70-84-75/0116-66-23-90
0221 11-21-22/0221-11-31-56
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
በኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የግብርና ውጤቶች ሽያጭና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ዘርፍ
