በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ከዚህ በታች የተገለፁትን ተሽከርካሪና ማሽነሪ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 006/2018
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ከዚህ በታች የተገለፁትን ተሽከርካሪና ማሽነሪ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
|
No. |
ltems |
Quantity |
|
1 |
Grader |
2 |
|
2 |
Dump truck |
2 |
ስለዚሀ በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች፡-
1. በአቅራቢዎች ዝርዝር የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
2. የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
3. በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ማቅረብ የሚችሉ።
4. የግብር ከፋይነት ሰርተፍኬት /Tin Number/ ያላቸው፡፡
5. ግብር ስለመክፈላቸው ከሚመለከተው አካል የተሰጣቸው የግብር ከፋይነት ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉ።
6. ማንኛውም ተጫራች የንግድ ፍቃዱን በማቅረብ ለጨረታው የተዘጋጀውን ሰነድ ሆሳዕና በሚገኘው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ የመንግሥት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት የግዥና ዋጋ ጥናት ዳይሬክቶሬት በመቅረብ የማይመለስ 500.00 /አምስት መቶ/ ብር በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
7. ጨረታው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 20 ቀናት አየር ላይ ይውላል፡፡
8. ተጫራቾች የጨረታ መወዳደሪያ ሀሳባቸውን ጋዜጣው ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ መጨረሻው 20ኛው ቀን ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ድረስ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ የመንግሥት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት የግዥና ዋጋ ጥናት ዳይሬክቶሬት ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
9. ጨረታው አየር ላይ መቆያው ጊዜ ባበቃበት ቀን 6፡00 ሰዓት ታሽጎ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
10. ጨረታው በጋዜጣ የሚውልበት የመጨረሻ ቀን በዓል፣ ቅዳሜ ወይም እሑድ የሚውል ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ከላይ በተገለጸው ተመሳሳይ ሰዓት ታሽጎ ይከፈታል፡፡
11. ተጫራቾች 600,000 /ስድስት መቶ ሺህ/ ብር የጨረታ ማስከበሪያ ማስያዝ አለባቸው፡፡
12. ቢሮው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 0910 92 89 86 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ የመንግሥት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት
/ሆሳዕና/
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ
