ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥር ድርጅት ለቢሮ አገልግሎት የሚውል ኤሌክትሮኒክሶች (ኮምፒውተር፣ ፕሪንተር፣ ፎቶ ኮፒ ማሽን) በሀገር አቀፍ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ መለያ ቁጥር 0001/2018
ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥር ድርጅት ለቢሮ አገልግሎት የሚውል ኤሌክትሮኒክሶች (ኮምፒውተር፣ ፕሪንተር፣ ፎቶ ኮፒ ማሽን) በሀገር አቀፍ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ በዚሁ መሰረት ተጫራቾች --
1. የዘመኑን ግብር የከፈሉና በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ማቅረብ የሚችሉ
2. የአቅራቢነት የምዝገባ ምስክር ወረቀት እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉ
3. ተጫራቾች ተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የተመዝጋቢነት ሰርተፍኬት ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
4. ተጫራቾች በጨረታ ሰነዱ ላይ የተዘረዘረውን እያንዳንዱን ዋጋ ሞልታችሁ / ፈርማችሁ እና የድርጅታችሁን ማህተም በማድረግ ፋይናንሻል ኦርጂናል ዶክመንት አንድ እና ፋይናንሻያል ኮፒ ሁለት ቴክኒካል ኦርጂናል አንድ እና ቴክኒካል ኮፒ ሁለት ለየብቻ በማድረግ በፖስታ አሽጋችሁ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ እስከ 15ኛው ቀን 8፡30 ድረስ በድርጅቱ ግዥና ንብረት አስተዳደር አገልግሎት ክፍል በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸኋል፡፡ ጨረታው ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15ኛው ቀን ከቀኑ 8፡30 ላይ ተዘግቶ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ 9፡00 ሰዓት ላይ ይከፈታል፡፡ 15ኛው ቀን የስራ ቀን ካልሆነ ጨረታው በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓትና ቦታ ተዘግቶ ይከፈታል።
5. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ (CPO) 50,000 (ሀምሳ ሺህ ብር ብቻ) ቴክኒካል ኦርጂናል ዶክመንት ውስጥ አስገብተው ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
6. ተጫራቾች የተዘጋጀውን ዝርዝር የጨረታ ሰነድ በነፃ ከድርጅቱ ግዥና ንብረት አስተዳደር አገልግሎት ክፍል ቀርበው መግዛት ይችላሉ፡፡
7. በጨረታው ሂደት አሸናፊው ድርጅት እቃዎቹን ቢሯችን ድረስ በማምጣት ማስረከብ ይኖርበታል፡፡
8. ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0912818102/0911995805 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የድርጅቱ አድራሻ ሆሳዕና ከተማ ወደ ወልቂጤ መውጫ መንገድ ካቶሊክ ት/ቤት ጎን ላይ ነው።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥር ድርጅት
