Tender Detail

Tender Details

  • Company የሸካ ዞን ማሻ ማረሚያ ተቋም
  • Address ሸካ ዞን ፡ ደቡብ ክልል ፡ ኢትዮጵያ, Phone: - - - - - - -
  • Website
  • Deadline04 Apr 2026, 12:00 AM
  • magazineAddis Zemen
  • Bid Document Price100.00
  • opening date2026-04-04 00:00:00
  • Categories Agriculture And Farming , Raw Materials , Products

ለሸካ ዞን ማሻ ማረሚያ ተቋም በስሩ ለሚገኙ የሕግ ታራሚዎች ቀለብ እህል ጥራጥሬና ሸቀጣሸቀጥ እና ለሲቪል ሠራተኞች ደንብ ልብስ ከሚያዚያ 1 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ሐምሌ 2018 ዓ.ም ለ120 ቀናት ከሚያቀርቡ ሕጋዊ ፍቃድ ካላቸው ድርጅቶች፣ አቅራቢ ነጋዴዎችና ማኅበራት በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።


የጨረታ ማስታወቂያ

 

ለሸካ ዞን ማሻ ማረሚያ ተቋም በስሩ ለሚገኙ የሕግ ታራሚዎች ቀለብ እህል ጥራጥሬና ሸቀጣሸቀጥ እና ለሲቪል ሠራተኞች ደንብ ልብስ ከሚያዚያ 1 ቀን 2018 . እስከ ሐምሌ 2018 . 120 ቀናት ከሚያቀርቡ ሕጋዊ ፍቃድ ካላቸው ድርጅቶች፣ አቅራቢ ነጋዴዎችና ማኅበራት በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።

በዚሁ መሠረት ተጫራቾች ማሟላት የሚገባቸው ግዴታዎች፡-

1. በየዘርፉ ሕጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸውና የታደሰ የዘመኑን ንግድ ፍቃድ ማቅረብ የሚችሉ

2. የተጨማሪ ዕሴት ታከስ ተመዝጋቢ የሆነና የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል

3 የጨረታው ተወዳዳሪዎች ለጨረታው ማስከበሪያ ለእህልና ጥራጥሬ ብር 50000/ ሃምሳ ሺህ ብር/ ለሸቀጣ ሸቀጥና ደንብ ልብስ ብር 20000 /ሃያ ሺህ ብር/ በጥሬ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ በማስያዝ የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100 በመክፈል ቢሮ ቁጥር 3 የጨረታ ሰነዱን መግዛት የሚችል፤

4. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ በሰም በታሸገ ፖስታ በማድረግ ፊርማና የድርጅቱን ማህተም ያለውን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 15 ተከታታይ የመንግሥት የሥራ ቀናት ለዚሁ ጨረታ አገልግሎት በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።

5. ጨረታው 16ኛው ቀን ከቀኑ 800 ሰዓት ላይ ታሽጎ 830 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎች ቢገኙም ባይገኙም ይከፈታል።

6. ጨረታው የሚከፈትበት ቀን የመንግሥት የሥራ ሰዓት ካልሆነ በሚቀጥለው ቀን በተመሳሳይ ቀንና ሰዓት ይከፈታል።

7. የጨረታው አሸናፊ የሆነው አቅራቢ ዕቃዎችን አጓጉዞ በራሱ ወጪ ለማሻ /ተቋም ማስረከብ የሚችል

8. ተጫራቾች አሁን ባቀረቡት ዋጋ 4 ተከታታይ ወር ማቅረብ የሚችል ሲሆን፤ በመሐሉ የድርድር ጥያቄ ተቀባይነት የለውም።

9. ተጫራቾች የውል ማስከበሪያ 10% ለማስያዝ ፈቃደኛ የሆነ

10. ተቋሙ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በሕግ የተጠበቀ ነው።

 

ሸካ ዞን ማሻ ማረሚያ ተቀም

 

Save Tender