የመተሐራ ስኳር ፋብሪካ ለሆስፒታል አገልግሎት የሚውሉ ከዚህ በታች በዝርዝር የተገለፁትን በዘርፍ ከተሰማሩ ሕጋዊ የመድኃኒትና የሕክምና መገልገያ አከፋፋዮችን ወይም አስመጪዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለአንድ ዓመት የሚቆይ ውል በማሰር ግዥ ማከናወን ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር MSF/LP/04/2026
የመተሐራ ስኳር ፋብሪካ ለሆስፒታል አገልግሎት የሚውሉ ከዚህ በታች በዝርዝር የተገለፁትን በዘርፍ ከተሰማሩ ሕጋዊ የመድኃኒትና የሕክምና መገልገያ አከፋፋዮችን ወይም አስመጪዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለአንድ ዓመት የሚቆይ ውል በማሰር ግዥ ማከናወን ይፈልጋል፡፡
· ጥቅል 1 : መድኃኒቶች (MEDCINES)
· ጥቅል 2፡ የላብራቶሪ ኬሚካሎችና ሪኤጀንቶች (LABORATORY CHEMICALS AND REAGENTS)
· ጥቅል 3 የተለያዩ የሕክምና መገልገያ መሣሪያዎች (MEDICAL SUPLLIES)
ስለሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉና ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተወዳዳሪዎች እንደሚከተለው ተጋብዛችኋል፡፡
1. በዘርፉ የተሰማራችሁ የመድኃኒትና የሕክምና አከፋፋዮችን ወይም አስመጪዎችን የ2018 ዓ.ም የታደሰ ሕጋዊ ንግድ ፍቃድ ያላችሁ እንዲሁም የዘመኑን የመንግሥት ግብር የከፈላችሁ፤ በመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ መመዝገባችሁን ማቅረብ የምትችሉ
2. ጉዳዩ ከሚመለከተውና አግባብነት ካለው መንግሥታዊ መሥሪያ ቤት የሙያ ፈቃድ ሰርተፊኬት፣ የጥራት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ፍቃድ
3. በጨረታው አሸናፊ የሆኑት ድርጅቶች ላሸነፉበት አይነት በየጊዜው በሚቀርብላቸው የግዢ ትዕዛዝ መሠረት የተለያዩ መድኃኒቶች፤ አላቂ እና ቋሚ የሕክምና መገልገያ መሣሪያዎች የላብራቶሪ ኬሚካሎች እና ሪኤጀንቶች የአቅርቦት አይነት አዲስ አበባ ፊሊፕስ ሕንፃ ቢሮ ቁጥር 215 ግዥ ቡድን ድረስ ማቅረብ የሚችሉ፤
4. የጨረታ ማስከበሪያ ብር ሃምሳ ሺ (50,000.00) በሲ.ፒ.ኦ /C.P.O/ ወይም የባንክ ዋስትና /Bid bond guarantee/ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
5. መተሐራ ስኳር ፋብሪካ ግዥ ቡድን አዲስ አበባ ሜክሲኮ አደባባይ ፊሊፕስ ሕንፃ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 215 ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት የንግድ ፈቃድ ይዘው በመቅረብ ለእያንዳንዱ ጥቅል የማይመለስ ብር 300.00 (ሦስት መቶ ብር) እየከፈሉ የጨረታውን ሠነድ በመውሰድ በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ፡፡
6. ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ በራሳቸው የዋጋ ማቅረቢያ (Proforma invoice) ላይ በማዘጋጀት በሰም በታሸገ ፖስታ በማድረግ እ.ኢት.ኢ ሚያዚያ 20 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጠዋቱ 4፡00 ሠዓት ድረስ መተሐራ ስኳር ፋብሪካ ግዥ ቡድን አዲስ አበባ ሜክሲኮ አደባባይ ፊሊፕስ ሕንፃ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 215 ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
7. ጨረታው በዕለቱ ሚያዚያ 20 ቀን 2018 ዓ.ም ከጧቱ 4፡30 ሰዓት ላይ ከላይ በተጠቀሰው አድራሻ ቢሮ ቁጥር 119 ውስጥ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
8. ፋብሪካው ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መበቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ስልክ ቁጥር 0115-505607፣ 0115505633 ሜክሲኮ አደባባይ ፊሊፕስ ሕንፃ አዲስ አበባ
የመተሐራ ስኳር ፋብሪካ
