የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ለሐረር ፌደራል ፖሊስ ሆስፒታል እና አፓርትመንት ፕሮጀክት ግንባታ አገልግሎት የሚውል የSupply and Fix Satellite dish system ግዥ ለመፈፀም ተጫራቾችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር. DCE/ SF/49/2026
የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ለሐረር ፌደራል ፖሊስ ሆስፒታል እና አፓርትመንት ፕሮጀክት ግንባታ አገልግሎት የሚውል የSupply and Fix Satellite dish system ግዥ ለመፈፀም ተጫራቾችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
|
የዕቃው አይነት |
የፕሮጀክት ስም |
የጨረታ ቁጥር |
የጨረታ መዝጊያ ቀን እና ሰዓት |
የጨረታ መክፈቻ ቀን እና ሰዓት |
የጨረታ መስከበሪያ |
|
Supply and Fix Satellite dish system |
ለሐረር ፌዴራል ፖሊስ ሆስፒታል እና አፖርትመንት ፕሮጀክት |
DCE/SF/49/2026 |
ሚያዝያ 9 ቀን 2018 ዓ.ም 4፡15 ሰዓት |
ሚያዝያ 9 ቀን 2018 ዓ.ም 4፡30 ሰዓት |
100,000.00 |
ስለሆነም፡-
1. ተጫራቾች በዘርፉ የተሰማሩ መሆኑን የሚገልጽ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡበት የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፣ በጨረታ ለመሳተፍ የሚሰጥ የታደሰ የምስክር ወረቀት (ታክስ ክሊራንስ) እና የሀገር ውስጥ ተጫራቾች በአቅረቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡ መሆኑን የሚያረጋግጥ ኮፒ ወዘተ_ ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው፡፡
2. ተጫራቾች ከላይ በሰንጠረዡ በተገለፀው መሰረት የጨረታ ማስከበሪያ Bid Bond ማቅረብ ይኖርበታል። የጨረታ ማስከበሪያው እንደ ተጫራቹ ምርጫ በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና (Unconditional bank Guarantee) ወይም በባንከ የተሰጠና የተረጋገጠ (C.P.O) ከመጫረቻ ሰነዳቸዉ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
3. ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ በጨረታ ሰነድ በተዘረዘረው ዝርዝር መሰረት መሆን ይኖርበታል
4. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200.00 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል ዘወትር በሥራ ሰዓት የግዥና አቅርቦት አስተዳደር መምሪያ ቢሮ መግዛት ይቻላል፡፡
5. ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን የጨረታ ቴክኒካል ሰነድ እና ዋጋ በታሸገ ኤንቨሎፕ ከላይ በሰንጠረዡ በተገለፀው ቀን እና ሰዓት በኢንተርፕራይዙ የግዥና አቅርቦት አስተዳደር መምሪያ ቢሮ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
6. ጨረታው በሰንጠረዡ በተገለፀው መሰረት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በድርጅቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
7. ኢንተርፕራይዙ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ቃሊቲ ቶታል ከአዲሱ ስታድየም ጀርባ ወይም ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ ት/ቤት አጠገብ
የቀጥታ ስልክ ቁጥር 0114-40-34-34 ማዞሪያ 0114-42-22-70/71/72
E-mail አድራሻ Infoadce-et.com የድረ-ገፅ አድራሻ www.dce-et.com
ፖ.ሳ.ቁ 3414
የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ
