Tender Detail

Tender Details

  • Company የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ፋይናንስ ቢሮ
  • Address በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 0910928986
  • Website
  • Deadline13 May 2026, 12:00 AM
  • magazineAddis Zemen
  • Bid Document Price500.00
  • opening date2026-05-13 00:00:00
  • Categories Vehicles Rent , Rent , Vehicle

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ የመንግሥት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ከዚህ በታች የተገለፁትን ተሽከርካሪዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።


የጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር 007/2018

 

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ የመንግሥት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ከዚህ በታች የተገለፁትን ተሽከርካሪዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።

No.

 

Items

 

Quantity

 

1

 

Double cabin pick up

 

2

 

2

 

Station wagon 9 seat hard top

 

2

 

3

 

Meat transporter van truck

 

2

 

 

ስለዚህ በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች፡-

1.     በአቅራቢዎች ዝርዝር የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ።

2.     የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።

3.     በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ማቅረብ የሚችሉ።

4.     የግብር ከፋይነት ሰርተፍኬት/Tin Number/ ያላቸው።

5.     ግብር ስለመከፈላቸው ከሚመለከተው አካል የተሰጣቸው የግብር ከፋይነት ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉ።

6.     ማንኛውም ተጫራች የንግድ ፈቃዱን በማቅረብ ለጨረታው የተዘጋጀውን ሰነድ ሆሳዕና በሚገኘው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ የመንግሥት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት የግዥና ዋጋ ጥናት ዳይሬክቶሬት በመቅረብ የማይመለስ 500.00/አምስት መቶ/ ብር በመክፈል መግዛት ይችላሉ።

7.     የጨረታ ማስታወቂያው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 20 ቀናት አየር ላይ ይውላል።

8.     ተጫራቾች የጨረታ መወዳደሪያ ሀሳባቸውን የጨረታ ማስታወቂያው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ መጨረሻው 20ኛው ቀን ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ድረስ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ የመንግሥት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት የግዥና ዋጋ ጥናት ዳይሬክቶሬት ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።

9.     ጨረታው አየር ላይ መቆያው ጊዜ ባበቃበት ቀን 6፡00 ሰዓት ታሽጎ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።

10.  ጨረታው በጋዜጣ የሚውልበት የመጨረሻ ቀን በዓል፣ ቅዳሜ ወይም እሑድ የሚውል ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ከላይ በተገለጸው ተመሳሳይ ሰዓት ታሽጎ ይከፈታል።

11.  ተጫራቾች 600,000/ስድስት መቶ ሺህ ብር/ የጨረታ ማስከበሪያ ማስያዝ አለባቸው።

12.  ቢሮው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በሕግ የተጠበቀ ነው።

ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 0910 928 986 በመደወል ማግኘት ይችላሉ።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ የመንግሥት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት

/ሆሳዕና/

 

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ

Save Tender

በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የዋና ስራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ግዥ ቡድን ለ2019 በጀት ዓመት አገልግሎት መጠቀሚያ የሚሆን በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰሩ ተሽ...

READ MORE