የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የዎርክ ሾፕ መሣሪያዎች እና የተለያዩ መኪናዎች መለዋወጫ እቃዎችን ለመግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
ከታች ቀጥሎ በሎት አንድ እና በሎት ሁለት የተዘረዘሩትን የዎርክ ሾፕ መሣሪያዎች እና የተለያዩ መኪናዎች መለዋወጫ እቃዎችን ለመግዛት የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ የጨረታ ቁጥር ኢግሥ.ኮ /በግጨ/12/2018
|
ተ.ቁ |
የሎት ቁጥር |
የጨረታ አይነት |
የጨረታ ሰነድ መሸጫ ዋጋ (የማይመለስ) ብር |
የጨረታ ማስከበሪያ ብር |
የጨረታ መዝጊያና መክፈቻ ቀንና ሰዓት |
||
|
የመዝጊያ ቀን |
የመዝጊያ ሰዓት |
የመክፈቻ ሰዓት |
|||||
|
1 |
ሎት አንድ |
የጥገና ዎርክ ሾፕ መሣሪያዎች |
200 |
100ሺህ |
ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ም |
4፡00 |
4፡30 |
|
2 |
ሎት ሁለት |
የተለያዩ መኪናዎች የመለዋወጫ እቃዎች ግዥ |
200 |
100ሺህ |
ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ም |
8፡00 |
8፡30 |
የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ከላይ በሠንጠረዥ ውስጥ በዝርዝር እንድተገለፀው እና ከጨረታ ሰነዱ ጋርበተያያዘው ቴክኒካል መስፈርት መሰረት ተጫራቾችን አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች፡-
1. በዘርፉ የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸሁ፤ ቲን ቫት፤ በGP/PPA የአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ ስለመመዝገባችሁ እንዲሁም ከገቢዎች ሚ/ር ከሊራንስ ማቅረብ የሚችሉ ተጫራቾች ዘወትር በሥራ ሰዓት ሳሪስ አቦ ፋፋ የምግብ እሚ አጠገብ የቀድሞው እርሻ መመሣሪያዎችና ቴክኒክ አገልግሎት አ.ማ. ግቢ የኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤት ግዥ ከፍል ቀርበው የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ከላይ በእያንዳንዱ ሎት በተገለፀው ብር መሰረት በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ ፡፡
2. ተጫራቾች የሚሞሉት ዋጋ በግልጽ የሚታይና ስርዝ ድልዝ የሌለበት መሆን ይኖርበታል፡፡
3. ተጫራቾች ለጨረታው ዋስትና (ለ60 ቀናት የሚቆይ) ማስከበሪያ ከላይ በተገለፀው መሰረት በሲ.ፒ.ኦ. ወይም በባንከ ጋራንቲ (unconditional) ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡ የጨረታ ዋስትናው ለብቻው በአንድ ፖስታ ውስጥ ተደርጎ ከኦርጂናል ቴክኒካል ሰነድ ጋር ተያይዞ መቅረብ ይኖርበታል፡፡ የጨረታው ዋጋ ለ60 ቀናት የጸና ይሆናል ፡፡
4. ተጫራቾች ከጨረታ ሰነዱ ጋር ተያይዞ በቀረበው ዶክመንት መሰረት እያንዳንዱ ሎት-1 እና በሎት-2 ለየብቻ በማድረግ ቴከኒካል ኦርጂናልና ኮፒ እንዲሁም ፋይናንሽያል በተለያዩ ፖስታ በማድረግ ፋይናንሽያል ሰነዱ ዋና እና ኮፒ በመለየት በታሸገ ኤንቨሎፕ አድርገው በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
5. ጨረታው የሚዘጋበት እና የሚከፈትበት ቀን እና ሰዓት ከላይ በሠንጠረዥ ውስጥ በተገለፀው መሰረት ሁኖ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በኮርፖሬሽኑ የመሰብሰቢያ አዳራሽ የቴክኒካል ጨረታ ሰነድ የመከፈቻ ስነሥርዓት ይከናወናል ፡፡
6. ኮርፖሬሽኑ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ ማብራሪያ፡- የኢትዮጵያ የገብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን
ስልክ ቁጥር:- +251911984467 /+251913217657
የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን
አዲስ አበባ
