የዳሽን ቢራ ምርቶችን ለማከፋፈል ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾችን አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም፡-
ዳሽን ቢራ ፋብሪካ አ.ማ ጎዴ ፣ጋሸና ፣ አዲግራት፣ አጣዬ፣ መካነሰላም እና ደላንታ መስመር የዳሽን ቢራ ምርቶችን ለማከፋፈል ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾችን አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም፡-
- በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያለው
- በቂ ተሽከርካሪ ማቅረብ የሚችል (የራሱ ቢሆን ይመረጣል)
- ምርቱን ለማከማቸት የሚሆን መጋዘን (የራሱ ቢሆን ይመረጣል)
- በዘርፉ ተዛማጅ የስራ ልምድ ያለው
- የስራ ማስኬጃ በቂ ካፒታል ያለው መሆኑን የሚያሳይ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ በአካባቢው ለረጅም ጊዜ ነዋሪ የሆነና በአካባቢው ማህበረሰብ መልካም ስም ያላቸው፤
- ማህበራዊ እና ህጋዊ ግዴታዎችን በአግባቡ እየተወጣ ያለና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፤
- ተጫራቾች ይህ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 7 (ሰባት) ተከታታይ ቀናት ውስጥ አስፈላጊውን ሠነድ አሟልተው አዲስ አበባ፣ ዳሽን ቢራ ፋብሪካ ዋና መስሪያ ቤት (22 የቱሪስት ንግድ ስራ ድርጅት አጠገብ) ከሚገኘው የድርጅቱ ቢሮ ለዚህ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ በብር 1000 (አንድ ሺ ብር) ገዝቶ በመሙላት ጨረታውን መሳተፍ የሚችሉ መሆኑን እየገለጽን::
- ጨረታው ከግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ግንቦት 27 2018 ዓ.ም ድረስ አየር ላይ የሚቆይ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
- ጨረታው ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ/ም ጠዋት 4:00 ተዘግቶ በዚያው እለት 4፡30 የሚከፈት ሲሆን ቀጣይ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) ቀናት ውስጥ ውጤቱን የምናሳውቅ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
- ዳሽን ቢራ ፋብሪካ አ.ማ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብት አለው፡፡
ከሠላምታ ጋር
