በአርሲ ዞን ማረሚያ ቤት ውስጥ ለሚገኙት የህግ ታራሚዎች የበሰለ ምግብ ወይም ለምግብ አቅርቦት የሚውል ጥሬ እህል እና የተለያዩ ማጣፈጫዎችን እንዲሁም የማገዶ እንጨት በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
በአርሲ ዞን ማረሚያ ቤት ውስጥ ለሚገኙት የህግ ታራሚዎች የበሰለ ምግብ ወይም ለምግብ አቅርቦት የሚውል ጥሬ እህል እና የተለያዩ ማጣፈጫዎችን እንዲሁም የማገዶ እንጨት የ2018 ዓ.ም በጀት ከሐምሌ 1/2018 ዓ.ም ጀምሮ እስክ ታህሳስ 30/2019 ዓ.ም ለ 6 ወር (ስድስት ወር) ለሚቆይ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ በዚህ መሰረት ማንኛውም ጨረታውን ለመካፈል የሚፈልግ ድርጅት ወይም ግለሰብ፡-
1. ተወዳዳሪዎች የገንዘብ እና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር ወይም ቢሮ ውስጥ የተመዘገቡና የዘመኑን የስራ ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ እና አግባብነት የለው 2018 የታደሰ የንግድ ስራ ፍቃድ ያላቸው መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡
2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) የተመዘገቡ ወይም የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ የሚያቀርቡ መሆን አለባቸው።
3. የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ) ከፍሎ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት የዞን ማረሚያ ቤት አስተዳደር ጽ/ቤት በመቅረብ መግዛት ይችላሉ።
4. ተጫራቾቹ የጨረታ ማስከበሪያ ከመቶ 2% በጥሬ ገንዘብ ወይም በተመሰከረለት ቼክ እና የምግብ እህል ናሙና ከጨረታ ሰነድ ጋር አያይዞ ማቅረብ አለባቸው።
5. በጥቃቅን እና አነስተኛ ተደራጅቶ የበሰለ ምግብ ለማቅረብ የሚቀርቡ ማህበራት ቅድሚያ ይሰጣቸዋል፡፡ ይህ ካልተገኘ በጥሬ እህል እናወዳድራለን፡፡
6. ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ የስራ ቀናት በአየር ላይ ውሎ በ16ኛው ቀን በስራ ቀን ከረፋዱ በ4፡00 ሰዓት ሳጥኑ ታሽጎ በዚሁ ቀን 4፡30 ሰዓት በዞን ማረሚያ ቤት አስተዳደር ጽ/ቤት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው እንዲሁም የህግ ታራሚ ኮሚቴዎች እና የማረሚያ ቤቱ ጨረታ ኮሚቴ አባላት በተገኙበት ይከፈታል፡፡
7. የዞኑ ማረሚያ ቤት አስተዳደር ጽ/ቤት የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
8. በጥቃቅን እና አነስተኛ ተደራጅቶ የበሰለ ምግብ ለማቅረብ የሚቀርቡ ማህበራት በማረሚያ ቤቱ ውስጥ በተዘጋጀ ማብሰያ ቤት ውስጥ ምግብ አብስሎ መቅረብ የሚችል፡፡
9. ማረሚያ ቤቱ የሚገኝበት ከተማ በአርሲ ዞን አሰላ ማረሚያ ቤት፡፡
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0223311040/0913439972
በኦሮሚያ ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የአርሲ ዞን ማረሚያ ቤት
