ጨረታ ማስታወቂያ የሀዋሳ ከተማ አስ/ፋ/ኢ/ል መምሪያ ለሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት በ2019 በጀት ዓመት በታቀደው መሠረት ለምከር ቤት አዳራሽ የማርግዳ ስከሪን(WAL SCREEN INDOOR) እና ጀነሬተር 30KPA እና ከዛ በላይ በአድስ ዘመን ጋዜጣ ማስታውቂያ አወዳድሮ በዘርፉ ፈቃድ ካላቸው ድርጅቶች መካከል በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ጨረታ ማስታወቂያ
የሀዋሳ ከተማ አስ/ፋ/ኢ/ል መምሪያ ለሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት በ2019 በጀት ዓመት በታቀደው መሠረት ለምከር ቤት አዳራሽ የማርግዳ ስከሪን(WAL SCREEN INDOOR) እና ጀነሬተር 30KPA እና ከዛ በላይ በአድስ ዘመን ጋዜጣ ማስታውቂያ አወዳድሮ በዘርፉ ፈቃድ ካላቸው ድርጅቶች መካከል በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
በዚህ መሠረት:-
1. የግድግዳ ስከሪን፣ሎት ምድብ (አንድ)
2. ጀኔሬተር 30 KPA እና ከዛ በላይ îሎት/ምድብ-02(ሁለት)
በዚህ መሠረት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ድረጅቶች መወዳደር ይችላሉ፡-
1. በዘርፉ ሕጋዊ ፈቃድ ያላቸው አቅራቢዎች -
2 በሥራ መስኩ ህጋዊ የታደስ ንግድ ፍቃድ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉና የዘመኑን ግብርመክፈላቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ !
3. የአቅራቢነት ምዝገባ ምስከር ወረቀት ማቅረብ አለባቸዉ
4. በጨረታው እንዲሳተፍ የታከስ ከሊራንስ ማቅረብ አለበት፤
5. የጨረታ ሰነዱን ከሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ፋይ/ኢኮ/ልማት መምሪያ ቢሮ አራተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 54 (ሃምሳ አራት) በመቅረብ ይህ ጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10/አስር/ ተከታታይ ቀናት ዉስጥ ቀርባችሁ ሰነድ በብር 500 (አምስት መቶ ብር) በመግዛት ዋጋ ሞልቶ ማቅረብ ይችላሉ።
6. ተጫራቾች ለሎት 01 የጨረታ ማስከበርያ ብር፣ 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) እንዲሁም ለሎት 02 ብር፣50,000 (ሃምሳ ሺህ ብር) በባንክ የተረጋገጠ የተመሰከረለት ሲፒኦ (cpo) ወይም ቢድ ቦንድ ከጨረታ ሰንድ ጋር ማቅረብ አለበት
7. ጨረታ ሰነዱ በሰም ለየብቻቸው በታሸገ ኤንቬሎፕ አንድ ኦሪጂናል እና ሁለት ኮፒ ፋይናንሻል እና ቴክኒካል እንድ ኦሪጂናል እና ሁለት ኮፒ ሰነዶችን አሟልቶ በመያዝ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 10 (አስር) ተከታታይ ቀናት በፋይ ኢኮ/ልማት/ መምሪያ ቢሮ ቁጥር 54 (ግዢ ኬዝ ቲም) ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
8. አስፈላጊ የሆኑ ቴክኒካል ጉዳዮች በሚሸጥ ሰነድ ውስጥ በተቀመጠው መስፈርት መሠረት የሚገመገም ስለሆነ በጥንቃቄ መዘጋጀት ይጠበቅበታል፡
9. የሚገዙት እቃዎች እስቶክ ውስጥ መኖራቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ጨረታው በሚከፈትበት ቀን መቅረብ አለበት (እስቶክ ውስጥ መኖሩ ግዴታ ነዉ)።
10. ጨረታው በ11ኛው ቀን ከቀኑ 3፡30 ሰዓት ታሽጎ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበትም ሆነ ባልተገኙበት ከቀኑ 4፡00 ሰዓት በቢሮ ቁጥር 54 ይከፈታል።ይህ ቀን በበዓላት ቅዳሜ ወይም እሁድ ከሆነ ቀጥሎ ባለው የሥራ ቀን በተመሣሣይ ሠዓት የሚታሸግና የሚከፈትበት ቀን ይሆናል። የበዓል ቀን ከሆነ ደግሞ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ጨረታው ይከፈታል ።
11. መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ _ ወይም _ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ስልክ ቁጥር:- 046-212-13-34
የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስና ኢኮ/ልማት መምሪያ
