በኦሮሚያ ክልል በቡኖ በደሌ ዞን የጮራ ወረዳ የቁምባቤ ከተማ ማዘጋጃ ጽ/ቤት በ2019 በጀት ዓመት ለከተማ ውስጥ ለውስጥ መንገድ ስራ የሚውል ዶዘር አይነቱ D8R ባለ 300 H/P እና ከዚያ በላይ የሆነ በጥሩ ይዞታ ላይ ያለ እ.ኤ.አ 2012 አመተ ምህረት በኋላ የተመረተ ማሽን በሰአት መከራየት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር BMQ 3/2018
በኦሮሚያ ክልል በቡኖ በደሌ ዞን የጮራ ወረዳ የቁምባቤ ከተማ ማዘጋጃ ጽ/ቤት በ2019 በጀት ዓመት ለከተማ ውስጥ ለውስጥ መንገድ ስራ የሚውል ዶዘር አይነቱ D8R ባለ 300 H/P እና ከዚያ በላይ የሆነ በጥሩ ይዞታ ላይ ያለ እ.ኤ.አ 2012 አመተ ምህረት በኋላ የተመረተ ማሽን በሰአት መከራየት ይፈልጋል።
በዚህ መሰረት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያማሉ ባለ ንብረቶችን በጨረታ ማወዳደር ይፈልጋል።
1. ተጫራቾች ማሽነሪዎችን የማከራየት ፈቃድ ያላቸውና በ2018 ዓ/ም ግብር የከፈሉ፣ ፈቃዳቸውን ያሳደሱና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
2. የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
3. የባለ ንብረትነት ማረጋገጫ ሰነድ /የመታወቂያ/ ኦሪጅናል ወይም ፎቶ ኮፒ ማቅረብ የሚችልና የማሽኑን ዴክላራሲዮን ማቅረብ የሚችል።
4. ለማሽኑ የሚያስፈልገውን ማንኛውንም ወጪ መሸፈን የሚችል።
5. የሚፈለገው ማሽን ብዛት 1 /አንድ/
6. የጨረታውን ሰነድ የማይመለስ 1079 (አንድ ሺህ ሰባ ዘጠኝ ብር) የጮራ ገቢዎች ቢሮ በቴሌ ብር ከፍለው ህጋዊ ደረሰኝ በመውሰድ ለጨረታው የተዘጋጀውን ሰነድ ከጮራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 5 መውሰድ ይችላሉ።
7. የጨረታውን ሰነድ ቴክኒካል ዶክመት አንድ ኦርጅናል 3(ሶስት) ፎቶ ኮፒ በተለያዩ ፖስታዎች በማሸግ እንዲሁም የፋይናንስ ሰነድ አንድ ኦርጅናል 3(ሶስት) ፎቶ ኮፒ በተለያዩ ፖስታዎች በሰም በማሸግ የተለያዩ የስራ ፈቃድና ማስረጃዎችን አያይዞ ማቅረብ የሚችል።
8. ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን 1/12/2018 ጀምሮ ለ21 የስራ ቀናቶች አየር ላይ የሚቆይ ሲሆን ጨረታው የሚከፈትበት ቀን 30/12/2018 ዓ.ም ህጋዊ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በጮራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት የቴክኒክ ኮሚቴና አማካሪ መሀንዲስ በተገኘበት በቢሮ ቁጥር 1 (አንድ) በ4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በ4፡30 ይከፈታል።
9. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 50000 (ሀምሳ ሺህ ብር) በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለበት።
10.ማሽኑ ከተበላሸ በሌላ ማሽን መተካት የሚችል ወይም ከተበላሸበት ቀን ጀምሮ በ7 (ሰባት) ቀናት መሃል ጠግኖ ወደ ስራ ለማስገባት የሚችል።
11.ማሽኑ ካለበት ቦታ እስከ ወረዳ፣ ከወረዳ እስከ ስራ ቦታ፣ ከስራ ቦታ ወደ ሌላ ስራ ቦታ ለማጓጓዝ ሙሉ ወጪውን በሙሉ መሸፈን የሚችል።
12.መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
በኦሮሚያ ክልል በቡኖ በደሌ ዞን የጮራ ወረዳ የቁምባቤ ከተማ ማዘጋጃ ጽ/ቤት
