በደ/ቡ/ም/ኢ/ህ/ክ/መ/ በቤንች ሸኮ ዞን በሼይ ቤንች ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2019 ዓ/ም በጀት ዓመት የመኪና መለዋወጫ ዕቃ ከነ ሰርቪስ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለማስጠገን ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
በደ/ቡ/ም/ኢ/ህ/ክ/መ/ በቤንች ሸኮ ዞን በሼይ ቤንች ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2019 ዓ/ም በጀት ዓመት የመኪና መለዋወጫ ዕቃ ከነ ሰርቪስ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለማስጠገን ይፈልጋል፡፡
በዚህ መሰረት በጨረታ ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች የሚከተሉትን መስፈርት ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።
- የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድና የዘመኑን ግብር የከፈሉበት ፣ንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያለው፣ የአቅራቢነት ምስክርወረቀት ቫት ተመዝጋቢ የሆነ፣ በማቅረብ በሼ/ቤ/ወ/ ገ/ጽ/ቤት የጨረታው ሰነድ በማይመለስ 500 ብር/አምስት መቶ ብር/ በመክፈል መግዛት ይጠበቅባቸዋል፡፡
- የታደስ የብቃት ማረጋገጫ በተገቢው ሁኔታ ማቅረብ የሚችል
- የጨረታ ማስከበሪያ ብር 50,000 ብር/ሃምሳ ሺህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ማስያዥ ይጠበቅበታል፡፡
- እያንዳንዱ ፖስታ በታሸገ ማህተም በመምታት በሙሉ አድራሻ በመጻፍ እና በመፈረም ኦርጅናል ኮፒ የሚል ጽሁፍ በግልጽ በሚታይ ቦታ መጻፍ አለበት፡፡
- ተጫራቹ ሁሉንም የዋጋ ማቅረቢያ ሰነዶች ላይ የተጫራቾች ህጋዊ ተወካይፊርማ እና እንዲሁም የደርጀቱ ማህተም መኖር አለበት፡፡
- ይህ ጨረታ በማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ስራ ቀናት ማንኛውም ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ ለአንድ ኦርጅናል እና ሁለት ኮፒ በማድረግ ማስገባት አለባቸው፡፡
- ጨረታ የሚታሸገው በማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 16ኛው ቀን በሼ/ቤ/ ወ/ፋ/ጽ/ቤት ቢሮ ቁ/ር 7 ታሽጎ ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ተወካይ በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- ጨረታው የሚከፈትበት ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 16ኛው በሼ/ቤ/ወ/ፋ/ጽ/ቤት ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ተወካዮች በተገኘው ይከፈታል፡፡
- የሼ/ቤ/ወ/ ፋ/ጽ/ቤት የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብት በህግ የተጠበቀ ነው፡፡
- ጨረታው ዋጋ ጸንቶ የሚቆይበት ጊዜ ጨረታው ከተከፈተበት ዕለት ለ30/ሰላሳ ቀናት/ ብቻ ይሆናል፡፡
- በተጫራቾች ተሞልተው የሚቀርቡ የመወዳደሪያ ሀሳብ እና ሌሎችም ተጨማሪ ማረጋገጫዎች የሚመለከተው ኃላፊ ፊርማና ማህተም ካልተደረገባቸው የቀረበው የመወዳደሪያ ሀሳብ ሊሰረዝ ይችላል፣
- ፅ/ቤታችን የመኪና መለዋወጫ ዕቃ ከነ ሰርቪስ ለማስጠገን የሚፈፅመው የተዘረዘሩትን ሁኔታዎችና የቴከኒካል መመዘኛዎች ከሚያሟሉት መካከል በመንግስት በግዥ አፈጻጸም መመሪያ መሠረት ዝቅተኛ ዋጋ ላቀረበው ተጫራች የግዥ ትዕዛዝ በመስጠት ይሆናል፣
- የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15(አስራ አምስት ቀን) ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ይሆናል፡፡
- አድራሻ፦ በደ/ም/ኢ/ህ/ክ/መንግስት ቤንች ሸኮ ዞን ሼይ ቤንች ወረዳ ፋይናስ ጽ/ቤት
ስልክ ቁጥር:- 0952424403/0917972404
በቤንች ሸኮ ዞን የሼይ ቤንች ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት
