የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ በራስ ኃይሉ የስፖርት ትምህርት እና ስልጠና ማዕከል የከርሰ ምድር ውሃ ቁፋሮ ሥራ ጨረታ በማውጣት ማጠናቀቁ ይታወቃል፡፡
በድጋሚ የወጣ ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ በራስ ኃይሉ የስፖርት ትምህርት እና ስልጠና ማዕከል የከርሰ ምድር ውሃ ቁፋሮ ሥራ ጨረታ በማውጣት ማጠናቀቁ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም የመስመር ዝርጋታ እና ተያያዥ ሥራዎችን በግልፅ ጨረታ በማወዳደር በዘርፉ ብቃት እና ፍቃድ ካላቸው አቅራቢዎች አወዳድሮ ለማሰራት ስለሚፈልግ ከታች በዝርዝር የተገለጹትን መስፈርቶችን የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፡-
- ተጫራቾች የዘመኑን በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ደረጃቸው G+1 መሆን ይኖርበታል፡፡
- ተጫራቾች የቫት ምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የግብር ከፋይ ሰርተፍኬት ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች በአቅራቢነት መመዝገባቸው የሚገልጽ ሰርተፍኬት ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ስፖርት ቢሮ” ስም በተሰራ ሲ.ፒ.ኦ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ የስራ ቀናት ዘወትር በስራ ሰዓት የማይመለስ ብር 400 /አራት መቶ ብር/ ለእያንዳንዳቸው በመክፈል ከቢሮአችን ከግዥ እና ንብረት አስተዳደር ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት በአዲሱ ህንጻ 3ተኛ ፎቅ ቢሮ በግራ ክንፍ ባለው ቢሮ በመቅረብ ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሰነዱን አሟልቶ ፋይናንሺያል ዶክመንት አርጂናል እና ኮፒ በተለያየ ፖስታ እንዲሁም ዲሁም ቴከኒካል ዶክመንት ኦርጂናል እና ኮፒ በተለያየ በታሸገ ፖስታ በማድረግ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 /አስራ አምስት / ተከታታይ የስራ ቀናት በግዥ ንብረት አስተዳደር ዳይሬከቶሬት ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሰነድ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው አየር ላይ በዋለ በ16ኛው የስራ ቀን በ4፡00 የጨረታ ሳጥኑ ታሽጎ በዚያው እለት ከጠዋቱ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በመስሪያ ቤቱ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል።
- የጨረታ አሸናፊው እንደታወቀ ለጨረታ ማስከበሪያ የተያዘው ገንዘብ ለአሸናፊዎች ከ 7 ቀን በኋላ ይመለሳል።
- የጨረታ አሸናፊው በተጫራቾች መመሪያ በተጠቀሰው መሰረት የጨረታ አሸናፊነቱ በጽሁፍ በተገለጸ በ7 /ሰባት/ ቀናት በኋላ አስፈላጊውን የውል ማስከበሪያ ገንዘብ በመያዝ ወዲያውኑ ወደ ስራ ክፍሉ መጥቶ ውል መፈረም አለበት ይህ ባይፈጸም የጨረታ አሸናፊነቱን በመሰረዝ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዘው ሲ.ፒ.ኦ ለመንግስት ገቢ ይደረጋል፡፡
- ቢሮው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0118-120778 አድራሻ፡- ቅድስት
ማርያም መንገድ ብሔራዊ ሙዚየም ጀርባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና
ስፓርት ቢሮ
