የአዳማ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በ28/02/2017 በዋለው ችሎት የፍ/ባለእዳ የሆነው ንብረት በአዳማ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ ደደቻ ወረዳ ውስጥ የሚገኝ መኖሪያ ቤት ስፋቱ 338.72 ካሬ ሜትር ፤ የካርታ ቁጥር 3006/94 የሆነ በፍ/ባለእዳ ስም ተመዝግቦ የሚገኝ የጨረታ መነሻ ዋጋ ግምቱ 5.306,997.30 (አምስት ሚሊዮን ሶስት መቶ ስድስት ሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና ሰባት ብር ከ30/100) በ14/04/2017 ከ3፡00 ሰዓት እስከ 6፡00 ሰዓት ግልጽ በሆነ ጨረታ እንዲሸጥ ታዟል፡፡ ስለሆነም ለመግዛት ፍላጎት ያላችሁ ተጫራቾች እንድትወዳደሩ ይጋብዛል።
የጨረታ ማስታወቂያ
በፍ/ባለመበት አቶ ጌታቸው ጆቴ እና በፍ/ባለእዳ አቶ ወንድወሰን ንጉሴ መካከል ያለውን የፍርድ አፈፃፀም በተመለከተ የአዳማ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በ28/02/2017 በዋለው ችሎት የፍ/ባለእዳ የሆነው ንብረት በአዳማ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ ደደቻ ወረዳ ውስጥ የሚገኝ መኖሪያ ቤት ስፋቱ 338.72 ካሬ ሜትር ፤ የካርታ ቁጥር 3006/94 የሆነ በፍ/ባለእዳ ስም ተመዝግቦ የሚገኝ የጨረታ መነሻ ዋጋ ግምቱ 5.306,997.30 (አምስት ሚሊዮን ሶስት መቶ ስድስት ሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና ሰባት ብር ከ30/100) በ14/04/2017 ከ3፡00 ሰዓት እስከ 6፡00 ሰዓት ግልጽ በሆነ ጨረታ እንዲሸጥ ታዟል፡፡ በመሆኑም ይህንን ቤት ለመግዛት ፍላጎት ያላችሁ ሰዎች በዚህ በተባለው ቀን ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት እስከ 6፡00 ሰዓት ጨረታ ስለሚካሄድ ንብረቱ በሚገኝበት ቦታ በአዳማ ከተማ ደደቻ አራራ ወረዳ ውስጥ ቦታው ድረስ በአካል በመገኘት ለመግዛት ፍላጎት ያላችሁ በጨረታ ከሚሸጠው ንብረት መነሻ ዋጋ ውስጥ 1/4ኛ ለጨረታ ማስከበሪያ የሚያዝ መሆኑን አውቃችሁ የመታወቂያ ወረቀታችሁን ይዛችሁ እንድትቀርቡ፡፡ በጨረታ ላይ ተወዳድሮ ያላሸነፈ ሰው ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዘው 1/4ኛ የሚመለስለት መሆኑን እንድትገነዘቡ የአዳማ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ያሳውቃል፡፡
የአዳማ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የፍ/ብሔር ጉዳይ ችሎት
