በፍ/ባለመብት ወ/ሮ ፍሬህይወት ሉሉ ኪዳኔ እና በፍ/ባለዕዳ አቶ ኤርሚያስ አባተ አስፋው መካከል ስላለው የአፈፃፀም ክስ ጉዳይ በመዝገብ ቁጥር 86410 የተሰጠውን ውሣኔ ለማስፈፀም በ 12/1/2015 ዓ.ም በዋለው ችሎት ውሳኔ ያሳረፈበት በድሬዳዋ አስተዳደር ቀበሌ 02 አስተዳደር ውስጥ የሚገኝ እና በቤት ቁጥር Qim2-0167 የሚታወቀው መኖሪያ ቤት በብር 204,389.74 /ሁለት መቶ አራት ሺህ ሶስት መቶ ሰማንያ ዘጠኝ ብር ከ74/100/ እንዲሸጥ የታዘዘ በመሆኑ ታህሳስ 5 ቀን 2017 ዓ.ም በጨረታ አወዳድሮ በሀራጅ መሸጥ አስፈልጓል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
በፍ/ባለመብት ወ/ሮ ፍሬህይወት ሉሉ ኪዳኔ እና በፍ/ባለዕዳ አቶ ኤርሚያስ አባተ አስፋው መካከል ስላለው የአፈፃፀም ክስ ጉዳይ በመዝገብ ቁጥር 86410 የተሰጠውን ውሣኔ ለማስፈፀም በ 12/1/2015 ዓ.ም በዋለው ችሎት ውሳኔ ያሳረፈበት በድሬዳዋ አስተዳደር ቀበሌ 02 አስተዳደር ውስጥ የሚገኝ እና በቤት ቁጥር Qim2-0167 የሚታወቀው መኖሪያ ቤት በብር 204,389.74 /ሁለት መቶ አራት ሺህ ሶስት መቶ ሰማንያ ዘጠኝ ብር ከ74/100/ እንዲሸጥ የታዘዘ በመሆኑ ታህሳስ 5 ቀን 2017 ዓ.ም በጨረታ አወዳድሮ በሀራጅ መሸጥ አስፈልጓል፡፡ ስለሆነም በዚሁ ቀን ከጠዋቱ 3፡00 እስከ 4፡00 ሰዓት ድረስ ባለው ጊዜ የተጫራቾች ምዝገባ ንብረቱ በሚገኝበት ቦታ የሚካሔድ ሲሆን ጨረታው በተጠቀሰው ቀን እና ንብረቱ በሚገኝበት ቦታ ከጠዋቱ 4፡30 እስከ 5፡30 ባለው ጊዜ ይከናወናል።
በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ሁሉ ማንነታችሁን የሚያረጋግጥ መታወቂያ በመያዝ ንብረቱ በሚገኝበት ቦታ በመገኘት መሳተፍ የምትችሉ ሲሆን የጨረታው አሸናፊ ጨረታውን ያሸነፉበትን ገንዘብ 1/4ኛውን ወዲያውኑ በሞዴል 85 በፍ/ቤቱ ፋይናንስ ከፍል ማስያዝ አለባቸው፡፡ ቀሪውን 3/4ኛ ገንዘብ ደግሞ ጨረታው በተካሔደ በ15 ቀናት ውስጥ አጠናቀው ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ይህ ባይሆን ቀድሞ የተያዘው ገንዘብ ለጨረታ የወጣው ወጪ ተቀንሶለት ቀሪው ለመንግስት ገቢ እንደሚሆን ሊገነዘቡ ይገባል፡፡
የድሬዳዋ ምድብ የፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት ፍትሐብሔር ችሎት
