የአዳማ ከተማ አስተዳደር በከተማው የሚገኘውን አዲስ ህንፃ የፅዳት ሥራውን /City Complex/Out sores/ በማድረግ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የአዳማ ከተማ አስተዳደር በከተማው የሚገኘውን አዲስ ህንፃ የፅዳት ሥራውን /City Complex/Out sores/ በማድረግ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
በዚህ ሥራ በዘርፉ ላይ የተሰማሩ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ፡-
- ተጫራቶች በዘርፉ ህጋዊ የንግድ ስራ ፈቃድ ያላቸው፤ የዘመኑን ግብር የከፈሉ፤ የዘመኑን ግብር ከፍለው ማጠናቀቃቸውንና ጨረታ ላይ እንዲሳተፉ የሚል ማስረጃ ከሃገር ውስጥ ገቢ ባለስልጣን ጽ/ቤት ማቅረብ አለባቸው::
- የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች ለእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ 200.00 (ሁለት መቶ ብር) በጽ/ቤቱ ስም ሲንቄ ባንክ በሂሳብ ቁጥር 1054551161211 ላይ ገቢ በማድረግ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ለ15 ተከታታይ የስራ ቀናት በጽ/ቤቱ የግዢ የስራ ሂደት ቢሮ በመቅረብ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN No.) የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፤
- በአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡና የምስክር ወረቀት ያላቸው፡፡
- ስርዝ ድልዝ ያለው ወይም በግልፅ የማይታይ ፅሁፍ ተቀባይነት የለውም፤
- ጨረታውን ያሸነፈው ተወዳዳሪ የውል ማስከበሪያ ያሸነፈበትን ዋጋ አስር ፐርሰንት ማስያዝ የሚችል መሆን አለበት፡፡
- ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ማስረጃዎች ኦሪጅናልና ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው::
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታውን ሰነድ በመግዛት የማይመለስለ 200.00 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል ከአዳማ ከተማ ገንዘብ ፅ/ቤት በሥራ ሰዓት መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ለሚያቀርቡት የጨረታ ዋጋ ማስከበሪያ CPO ብር 10,000.00 (አስር ሺህ ብር) በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ለተደራጁ የትኛውንም የዋስትና ደብዳቤ የማንቀበል መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ዋናውንና ፎቶ ኮፒውን በታሸገ ኤንቨሎፕ ለጨረታ በተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው የሚከፈተው ማስታወቂያው ከወጣበት በ16ኛው ቀን የስራ ቀን ከሆነ በ8:00 ሰዓት ተዘግቶ በዛው ቀን በ8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአዳማ ከተማ ገንዘብ ቤት ሶስተኛ ፎቅ ግዢ እና ንብረት አስተዳደር ክፍል ውስጥ ይከፈታል፡፡ ዕለቱ በዓል ወይም መ/ቤቱ ዝግ ከሆነ በቀጣዩ የስራ ቀን በተጠቀሰው ሰዓት ጨረታው ይከፈታል፡፡
- መስሪያ ቤቱ ከሚያደርገው የግዢ ውል 20 ፐርሰንት መጨመር ወይም መቀነስ የሚችል መሆኑን ተጫራቹ መገንዘብ አለበት፡፡
- መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ በስልከ ቁጥር ፡- 022-2-11-14-42 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡
ስልክ ቁጥር ፡- 022-1-16-16-44/ 22-39
የአዳማ ከተማ ገንዘብ ጽ/ቤት
