በሸገር ከተማ በገላን ክፍለ ከተማ የገላን ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በገላን ወረዳ አስተዳደር ስር ላሉ ሴክተር መስሪያ ቤቶች ለ2019 በጀት ዓመት አገልግሎት የሚውሉ፡- የቢሮ የጽህፈት መሳሪያዎችን፡ የቢሮ ፈርኒቸር እቃዎችን፡ ኤሌክትሮኒክስ እቃዎችን፣ የጽዳትና አላቂ የቢሮ እቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር ገ/ወ/ገ/ቤት 002/2019
በሸገር ከተማ በገላን ክፍለ ከተማ የገላን ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በገላን ወረዳ አስተዳደር ስር ላሉ ሴክተር መስሪያ ቤቶች ለ2019 በጀት ዓመት አገልግሎት የሚውሉ፡- የቢሮ የጽህፈት መሳሪያዎችን፡ የቢሮ ፈርኒቸር እቃዎችን፡ ኤሌክትሮኒክስ እቃዎችን፣ የጽዳትና አላቂ የቢሮ እቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም በጨረታው ለመሳተፍ፦
- በዘርፉ ህጋዊ የታደሰ የንግድ ፍቃድ፤ የግብር መለያ ቁጥር እና የመንግስት ግብር ለመከፈላቸው ከግብር ሰብሳቢው መስሪያ ቤት ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- በአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡና የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ እና ማቅረብ የሚችሉ።
- ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት እለት አንስቶ ለ15/ለአስራ አምስት/ የስራ ቀናት ለእያንዳንዳቸው የጨረታ ሰነድ በማይመለስ ብር 400 /አራት መቶ ብር/ በገላን ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት ሲንቄ ባንክ ቁጥር 1064793701213 በመከፈል የጨረታውን ሰነድ ከገላን ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ዋጋ በመሙላት ኦርጅናል እና ኮፒ ለየብቻ በፖስታ በማሸግ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 16ኛው /አስራ ስድስተኛው/ የስራ ቀናት በገላን ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ለዚሁ አገልግሎት በተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ ከረፋዱ እስከ 4፡00 ሰዓት ብቻ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው በአስራ ስድስተኛው የስራ ቀን ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ እለት ከረፋዱ 4፡30 በገላን ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ሆኖም ጨረታው በሚከፈትበት ሰዓት ተጫራቾች ባይገኙም ጨረታውን ከመከፈት አያግደውም፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የሚውል በባንክ በተረጋገጠ / C.P.O/ሲፒኦ/ብቻ ለቢሮ ጽህፈት መሳሪያዎች 30,000/ሰላሳ ሺህ/ ለቢሮ ቋሚ ፈርኒቸር 20,000/ሀያ ሺህ/ ለኤሌክትሮኒክስ እቃዎች 30,000/ሠላሳ ሺህ/ ለቢሮ ጽዳት እና አላቂ እቃዎች 20,000/ሀያ ሺህ/ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ጨረታው ከተከፈተ በኋላ ከጨረታው ራሳቸውን ማግለል አይችሉም፡፡
- ተጫራቾች በጨረታው ሰነድ ዝርዝር መሰረት ሞልተው መመለስ ይኖርባቸዋል እንዲሁም ለሚወዳደሩባቸው እቃዎች ናሙና/sample/ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ መረጃ ስልክ ቁጥር:-
0913321839/0910742350/0911827152
በገላን ክፍለ ከተማ የገላን ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት
