የሀድያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለዞኑ ግብርና መምሪያ የሚያስፈልጉ የተለያዩ ዓይነት የእንስሳት መድኃኒትና መገልገያ ቁሳቁስ ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የሀድያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለዞኑ ግብርና መምሪያ የሚያስፈልጉ የተለያዩ ዓይነት የእንስሳት መድኃኒትና መገልገያ ቁሳቁስ ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
በዚሁ መሠረት ተጫራቾች ፡-
1ኛ. በመስክ የታደሰ ንግድ ፈቃድ
2ኛ. የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር
3ኛ. የዕቃ አቅራቢነት ሰርትፍኬት ያላቸው ድርጅቶች፤
በሀድያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ቢሮ ቁጥር 17 በአካል በመቅረብ የተዘጋጀው የጨረታ ሰነድ ብር 200 ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል እንድትገዙና ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና 20,000 /ሃያ ሺህ ብር/ በባንክ የተረጋገጠ (CPO) ማስያዝ የሚጠበቅባቸው ሲሆን የጨረታ መወዳደሪያ መምሪያው ባዘጋጀው ፎርማት ላይ ብቻ በመሙላት ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት የመወዳደሪያ ፖስታዎችን ኦርጅናልና ኮፒ በማሸግ ቢሮ ቁጥር 17 ላይ በሚገኘው የጨረታ ሳጥን ውስጥ እንድትገቡና ጨረታውም በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ላይ የጨረታ ሳጥን ታሽጎ በ4፡30 ሰዓት ላይ የሚከፈት ሲሆን ቀኑ የእረፍት ወይም የበዓል ቀን ከሆነ በቀጣዩ ቀን በተመሳሳይ ቦታና ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 0461784281/0465552337 ደውሉ መጠየቅ የሚቻል መሆኑን እንገልጻለን፡፡
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የሀድያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ
