በአዲስ አበባ ከተማ የመንግሥት ልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለሥልጣን ከነማ ፋርማሲዎች ድርጅት የጅምላ ንግድ አከፋፋይ አገልግሎት የመድኃኒት እና የሕክምና መገልገያዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል
የብሔራዊ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 001/2019
በአዲስ አበባ ከተማ የመንግሥት ልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለሥልጣን ከነማ ፋርማሲዎች ድርጅት በአዲስ አበባ ከተማ እና በዙሪያዋ ለሚገኙ ነዋሪዎች ለሁሉም ክ/ከተሞች ጤና መድኅን ተጠቃሚዎች ለፌዴራል ጤና መድኅን ተጠቃሚዎች መንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ላልሆኑ ድርጅቶች ጥራታቸውና ፈዋሽነታቸው የተረጋገጡ መድኃኒቶች እና የህክምና መገልገያዎችን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ በ53 መድኃኒት ቤቶች እና የጅምላ ንግድ አከፋፋይ ድርጅቶች የዱቤ / credit እና የጥሬ ገንዘብ / cash ሽያጭ አገልግሎት እየሰጠ ያለ የመንግሥት የልማት ድርጅት ነው፡፡ ስለሆነም ድርጅታችን ከነማ ፋርማሲ የጅምላ ንግድ አከፋፋይ አገልግሎት የመድኃኒት እና የሕክምና መገልገያዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት የሚፈልግ በመሆኑ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርት የምታሟሉ የሀገር ውስጥ የመድኃኒት አምራች እና የመድኃኒት አስመጪ የሆናችሁ ተወዳዳሪዎች በጨረታው መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
በንግድ ዘርፍ ወይም በመስኩ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያለው እና የቲን ማስረጃዎች፡
ተጫራቾች የማይመለስ ብር 1000 (አንድ ሺ ብር) በመክፈል ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት የመጀመሪያ ቀን ጀምሮ ለ 15 ተከታታይ የሥራ ቀናት (ቅዳሜን ግማሽ ቀን ጨምሮ ) ጉለሌ ክ/ከተማ ሰሜን ማዘጋጃ አካባቢ SMSS /ኤስ ኤም ኤስ ኤስ/ ሕንፃ 3ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 306 በመቅረብ የጨረታ ሰነድ መግዛት ይችላሉ።
ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ማስታወቂያው አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ እስከ 16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት የሚቻል ሲሆን 4፡30 ሰዓት የጨረታው ሳጥን የሚታሸግ ሰለሆነ አርፍዶ የሚመጣ ተቀባይነት የለውም፡፡ በዚሁ ቀን ከጠዋቱ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የጨረታው ሳጥን በድርጅቱ ግዥ ዳይሬክቶሬት ክፍል 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 403 የሚከፈት ይሆናል።
ማሳሰቢያ፡-
v ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
v ይህ የጨረታ ማስታወቂያ አየር ላይ በዋለበት ቀን በዋና መ/ቤት ማስታወቂያ ቦርድ እንዲሁም በተለያዩ የበይነ መረብ አማራጮች በምናሳውቀው ቀንና ሰዓት መሠረት ከተጫራቾች ጋር የቅድመ ጨረታ ስብሰባ የሚካሄድ መሆኑን እንገልፃለን።
አድራሻ፡- ከፒያሳ ወደ አዲሱ ገበያ በሚዎስደው መንገድ ሰሜን ማዘጋጃ አካባቢ SMSS / ኤስ ኤም ኤስ ኤስ / ሕንፃ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 403፤
የሥራ ሰዓት፡- ከሰኞ እስከ ዓርብ ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት እስከ 6:00 ሰዓት ከሰዓት ከ7፡00 ሰዓት እስከ 11:00 ሰዓት ቅዳሜ ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት እስከ 6፡00 ሰዓት
ለተጨማሪ መረጃ ስልክ ቁጥር 011-1-72-71-37
በአዲስ አበባ ከተማ የመንግሥት ልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለሥልጣን ከነማ ፋርማሲዎች ድርጅት
