ድርጅታችን የኢትዮጵያ የደረጃዎች ኤጀንሲ ያወጣውን የጥራት መስፈርት የሚያሟሉ እና ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ሸቀጦች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የሸቀጥ ግዥ ጨረታ (ቁጥር 004/2017)
ድርጅታችን የኢትዮጵያ የደረጃዎች ኤጀንሲ ያወጣውን የጥራት መስፈርት የሚያሟሉ እና ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ሸቀጦች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
- አንደኛ ደረጃ የበለፀገ የዳቦ ዱቄት CES 309:2022
- ፖስታ CES 1055:2022
- ሩዝ ES ISO 7301:2022
- ከሸንኮራ አገዳ የተመረተ ስኳር ICUMSA 45 (SUGAR CANE)
- ፈሳሽ የሱፍ ዘይት (CES17:) and labeling CES 73
- የተለያየ መጠን ያላቸው ከጥጥ የተመረተ የአንሶላ ምርቶች
- የተለያዩ መጠን ያላቸው የብርድ ልብስ ምርቶች (ES3840:2015)
- የተለያየ መጠን ያላቸው ፎጣዎች
- የፕሪንተር ወረቀት ES3735-15:2020
- የቆርቆሮ እና ግድግዳ ሚስማር
- የተለያየ መጠን ያላቸው የልብስ ማጠቢያ ሳሙናዎች CES42:2021 በጨረታው መካፈል የሚፈልጉ ተጫራቾች
- ለሩዝ፣ ስኳር፣ ፈሳሽ ዘይት እና ፕሪንተር ወረቀት አምራች ወይም አስመጭና አከፋፋይ እንዲሁም ለተቀሩት ምርቶች አምራች ብቻ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡
- በዘርፉ የታደሰ የንግድ ስራ ፍቃድ፣ የንግድ ምዝገባ ፈቃድ፤ ተጨማሪ ዕሴት ታክስ የተመዘገቡ፣ የግብር ከፋይነት ምዝገባ ሠርተፍኬት እና የግብር ክሊራንስ ያላቸው መሆን ይገባቸዋል፡፡
- ለጨረታ የተዘጋጀውን ዝርዝር የጨረታ ሠነድ የማይመለስ ብር 200.00 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል ቢስ መብራት ከሚገኘው የድርጅቱ ዋና መስሪያ ቤት የኢንዱስትሪ ውጤቶች ግዥ ዳይሬክቶሬት ቢሮ በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ለእያንዳንዱ ምርት በጨረታ ሰነዱ ላይ በተጠቀሰው መሰረት) ለብቻው በታሸገ ኤንቬሎፕ በማድረግ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- የጨረታ መወዳደሪያ ዋጋቸውን (financial) ና ከላይ ከተጠቀሱት ህጋዊ ሠነዶች (technical) በተለያየ የታሸገ ኤንቨሎፕ አንድ ኦሪጅናል እንዲሁም አንድ ኮፒ በማድረግ እስከ የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡00 ሠዓት ድረስ ማቅረብ ይችላሉ፡፡
- ጨረታው በተመሳሳይ የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡00 ሠዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ከጨረታ መዝጊያ ሰዓቱ በኋላ የሚቀርብ ሰነድ ተቀባይነት የለውም፡፡
ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ስልክ ቁጥር 0113692436
www.eiide.com.et.com.et
የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የኢንዱስትሪ ውጤቶች ግዥ ዳይሬክቶሬት
