በፍ/ባለመብት ወሮ ሃና በቀለ መንገሻ እና በፍ/ባለዕዳ አቶ ብርሃኑ ድንቄ ዶራ መካከል ስላለው የአፈፃፀም ክስ ጉዳይ በድሬዳዋ ከተማ በቀበሌ 04 ክልል ውስጥ የሚገኘው የቤት ቁጥሩ 0580 የሆነ ቤት እና ቦታ በጨረታ አወዳድሮ በሐራጅ መሸጥ አስፈልጓል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
በፍ/ባለመብት ወሮ ሃና በቀለ መንገሻ እና በፍ/ባለዕዳ አቶ ብርሃኑ ድንቄ ዶራ መካከል ስላለው የአፈፃፀም ክስ ጉዳይ በመዝገብ ቁጥር 96904 የተሰጠውን ውሣኔ ለማስፈፀም በድሬዳዋ ከተማ በቀበሌ 04 ክልል ውስጥ የሚገኘው የቤት ቁጥሩ 0580 የሆነ ቤት እና ቦታ መነሻ ግምቱ ብር 686,890.49 /ስድስት መቶ ሰማንያ ስድስት ሺህ ስምንት መቶ ዘጠና ብር ከ49/100/ እንዲሸጥ የታዘዘ በመሆኑ 11/8/2017 ዓ.ም በጨረታ አወዳድሮ በሐራጅ መሸጥ አስፈልጓል፡፡ ስለሆነም በዚሁ ቀን ከጠዋቱ 3፡00 እስከ 4፡00 ድረስ ባለው ጊዜ የተጫራቾች ምዝገባ ንብረቱ በሚገኝበት ቦታ የሚካሄድ ሲሆን ጨረታው በተጠቀሰው ቀን እና ንብረቱ በሚገኝበት ቦታ ከጠዋቱ 4፡30 እስከ 5፡30 ባለው ጊዜ ይከናወናል፡፡ ተጫራቾች የጨረታውን ሩብ በሲፒኦ ገቢ ያደረጉበትን መረጃ ያደረጉበትን መረጃ በመያዝ እንዲጫረቱና በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ሁሉ ማንነታችሁን የሚያረጋግጥ መታወቂያ በመያዝ ንብረቱ በሚገኝበት ቦታ በመገኘት መሳተፍ የምትችሉ ሲሆን፤ የጨረታው አሸናፊ ጨረታውን ያሸነፉበትን ገንዘብ 1/4ኛውን ወዲያውኑ በሞዴል 85 በፍ/ቤቱ ፋይናንስ ክፍል ማስያዝ አለባቸው፡፡ ቀሪውን 34ኛ ገንዘብ ደግሞ ጨረታው በተካሔደ በ15 ቀናት ውስጥ አጠናቀው ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ይህ ባይሆን ቀድሞ የተያዘው ገንዘብ ለጨረታ የወጣው ወጪ ተቀንሶለት ቀሪው ለመንግስት ገቢ እንደሚሆን ሊገነዘቡ ይገባል፡፡
የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት
የድሬዳዋ ምድብ ፍ/ብሔር ችሎት
