የጋምቤላ ህዝቦች ብሄራዊ ከልላዊ መንግስት ፋይናንስ ቢሮ በ2017 በጀት ዓመት Desktop computer መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 0003/2017
የጋምቤላ ህዝቦች ብሄራዊ ከልላዊ መንግስት ፋይናንስ ቢሮ በ2017 በጀት ዓመት Desktop computer መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች
-
በዘመኑ የታደሰ ፈቃድ ማቅረብ የሚችል
-
የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ያለው
-
የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል
-
የዘመኑን ግብር የከፈሉ ስለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ
-
ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር ከ1 እስከ 4 የተጠቀሱትንና ሌሎች ጠቃሚ ናቸው የሚሏቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሠነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
-
ተጫራቾች የጨረታ ሠነዱን ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ ቀናት የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ግዥ፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክተር ቢሮ ቁጥር 30 ቀርበው የማይመለስ ብር 500.00 ከፍለው መግዛት ይችላሉ፡፡
-
ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለሚወዳደሩበት የገንዘብ መጠን ወይም ጠቅላላ ዋጋ 10 በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲ.ፒ.ኦ) ማስያዝ አለባቸው::
-
ተጫራቾች በጨረታ ሠነዳቸው ላይ የተወዳዳሪውን ስም አድራሻ የሚመለከት (ህጋዊ) ወኪል የፈረመበት የተሟላና ማህተም ያረፈበት መሆኑን አረጋግጠው ማቅረብ አለባቸው።
-
ይህ ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 ተከታታይ የካላንደር ቀናት አየር ላይ ይቆያል፡፡ የጨረታው ሳጥን በ11ኛው ቀን ከቀኑ 9፡30 ታሽጎ በዚሁ ቀን 10፡00 ሰዓት ላይ የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ የግዥ፣ ንብረትና ፋይናንስ አስተዳደር ዳይሬክቶር የቢሮ ቁጥር 30 ይከፈታል። 10ኛው እና 11ኛው ቀን የሚውለው ቅዳሜና እሁድ ወይም የህዝብ በዓላት ቀን ላይ ጨረታው በሚቀጥለው የስራ ቀን በ10፡30 ሰዓት ተዘግቶ ከላይ በተባለው ሰዓት ይከፈታል፡፡
-
ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ ዋናውንና ኮፒውን በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ማቅረብ ይኖርበታል።
-
ቢሮው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ መረጃ፦ በስልክ ቁጥር 0475510827 በመደወል ማብራሪያ መጠየቅ የሚቻል መሆኑን እንገልጻለን።
የጋምቤላ ሕዝቦች ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ፋይናንስ ቢሮ
