የአ/ምንጭ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት የውሃ ማሸጊያ የመሠረት ግንባታ ሥራውን አጠናቆ የጣሪያ ክዳን ሙሉ ሥራዎችን ከነማቴሪያል አቅርቦትና የመግጠም ሥራ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለማሠራት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የአ/ምንጭ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት የውሃ ማሸጊያ የመሠረት ግንባታ ሥራውን አጠናቆ የጣሪያ ክዳን ሙሉ ሥራዎችን ከነማቴሪያል አቅርቦትና የመግጠም ሥራ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለማሠራት ይፈልጋል፡፡ በዚህም መሰረት
1ኛ. የውሃ እሸጋ ፋብሪካ የጣሪያ የማምረትና የመግጠም ሥራዎች
2ኛ. ከላይ በተራ ቁጥር አንድ በተጠቀሰው የሥራ ዘርፍ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያለውና የዘመኑን የመንግስት ግብር የከፈለ እንዲሁም በዘርፉ በቀጥታ ተሳታፊ መሆኑን የሚገልፅ ማስረጃ ያለው
3ኛ. ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር (በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽንና ዲዛይን ቁጥጥር ድርጅት ቢሮ) የተመዘገቡ ፈቃድ መኖሩን የሚገልፅ የምዝገባና የምሰክር ወረቀት ማቅረብ የሚችልና የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆናቸውንና የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር /TIN/ መኖሩን የሚገልጽ ማስረጃ እና ሌሎችን መረጃዎች አሟልቶ ማቅረብ የሚችል መሆን አለበት፡፡
4ኛ. ተጫራቾች በጨረታው ሠነድ ላይ የተዘረዘሩትን በትክክል አይተው ዋጋውን መሙላት አለባቸው::
5ኛ. ተወዳድሮ ሲያሸንፍ ወዲያውኑ ከድርጅቱ ጋር ውል ገብቶ ሥራ መሥራት የሚችል መሆን አለበት ፡፡
6ኛ. ተጫራቹ ለግንባታ ሥራ የሚያስፈልጉ ማቴሪያል ሲያቀርብ ወደ ሥራ ከመግባታቸው በፊት እያንዳንዱን ማቴሪያል በድርጅቱ ባለሙያ ጥራቱ እንዲረጋገጥ ማስደረግ አለበት፡፡
7ኛ. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከተፈቀደላቸው ከታወቁ ባንኮች ብር 200.000 /ሁለት መቶ ሺህ ብር / በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ cpo ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋሰትና ከጨረታ ዶክመንት ጋር ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
8ኛ. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 500 /አምስት መቶ ብር/ ከፍሎ ከድርጅቱ በመውሰድ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ/ፖስታ/ቴክኒካል ዶክመንት ኦርጅናል ለብቻ ቴክኒካል ዶክመንት ኮፒ ለብቻ እንዲሁም ፋይናንሻል ዶክመንት ኦርጅናል ለብቻ ፋይናንሻል ዶክመንት ኮፒ ለብቻ አሽጎ ለጨረታ በተዘጋጀ ሣጥን ውስጥ በማስገባት መወዳደር የሚችሉ ሲሆን ጨረታው በአርባምንጭ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ግቢ በ16ኛው ቀን ተጫራቾች /ህጋዊ ተወካዮቻቸው በተገኙበት በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከቀኑ በ8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በ8፡30 ላይ የሚከፈት ይሆናል፡፡ ሆኖም የጨረታ መዝጊያና መክፈቻ ቀን ቅዳሜና እሁድ ወይንም የበዓላት ቀን ላይ ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን መዝጊያና መክፈቻ ይሆናል ፡፡
9ኛ. በሌላ ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ ተቀባይነት የለውም።
10ኛ. መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው ::
ለበለጠ መረጃ የስልክ ቁጥር:- 0468810369/0468812049 መደወል ይቻላል ፡፡
በደ/ኢ/ብ/ብ/ህ/ክ/መንግሥት በጋሞ ዞን የአ/ም/ከ/ው/አ/ ድርጅት
