በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የአዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ ለተለያዩ የድርጅቱ መኪኖች የሚሆን ጎማ ከነ ኢነርቲዩብ እና ፍላፕ 235/80 R16 (bridge stone), 12 × 20 triangle,750x16 (bridge stone) Fuel filter primary ff200B, Fuel filter secondary MA005 ማቅረብ የሚችል ተወዳዳሪ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
ጨረታ ቁጥር አ.መ.ኬ.ፋ 007/2017
በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የአዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ ለተለያዩ የድርጅቱ መኪኖች የሚሆን ጎማ ከነ ኢነርቲዩብ እና ፍላፕ 235/80 R16 (bridge stone), 12 × 20 triangle,750x16 (bridge stone) Fuel filter primary ff200B, Fuel filter secondary MA005 ማቅረብ የሚችል ተወዳዳሪ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል። አስፈላጊው ዝርዝር መረጃና ቁጥራቸው በጨረታ ሰነዱ ላይ ተቀምጧል
- ማንኛውም ብቁ የሆኑ ተጫራቾች የ2017 ዓ.ም ህጋዊ የታደሰ ንግድ ፈቃድ የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ የምስክር ወረቀት ቫት ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚገልጽ ፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆኑን የሚገልጽ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው።
- ተጫራቾች ዝርዝር መግለጫ የያዘውን የጨረታ ሰነድ ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት ከአዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ ዋና መስሪያ ቤት እና በአዲስ አበባ ሳሪስ አቦ መርቲ ህንጻ በሚገኘው ቅርንጫፍ መ/ቤት የማይመለስ ብር 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል መግዛት ይቻላል።
- ተጫራቾች ለጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ የቀረበውን ዋጋ 2% በባንክ በተረጋገጠ ሲ.ፒ.ኦ ወይም በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ ማስያዝ ይኖርባቸዋል። ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን ቴክኒካል እና ፋይናንሽያስ ኦፈር ኦርጅናልና ኮፒ ለየብቻ በማሸግ ጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 ተከታታይ ቀናት በአዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ ዋና መስሪያ ቤት ወይም ቅርንጫፍ በአዲስ አበባ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው ሚያዝያ 28/8/2017 ከጠዋቱ 5፡00 ተዘግቶ በእለቱ ሚያዝያ 28 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 5፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአዋሽ መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ ዋናው መስሪያ ቤት ይከፈታል።
- ድርጅቱ/ፋብሪካው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ አድራሻ
ሞባይል 0920935336 ስልክ ቁጥር፦ 0222250266
በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የአዋሽ
መልካሳ ኬሚካል ፋብሪካ
