Tender Detail

Tender Details

  • Company በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት የአበበ ቢቂላ ጤና ጣቢያ
  • Address ከግሩም ሆስፒታል 300 ሜትር በኮብልስቶን ገባ ብሎ ፡ አዲስ አበባ ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 0112 73 20 81
  • Website
  • Deadline07 May 2025, 12:00 AM
  • magazine
  • Bid Document Price
  • opening date2025-05-07 00:00:00
  • Categories Wood And Wood Working , Used Items

የአ/ከ/ክ/ከ/ወ/05 አበበ ቢቂላ ጤና ጣቢያ በግልጽ ጨረታ የተለያዩ ያገለገለ የቢሮ መገልገያ እቃዎችን እንዲሁም አልጋዎችን ባሉበት ሁኔታ አወዳድሮ በግልፅ ጨረታ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡


 

የጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር 01/2016

 

የአ/////05 አበበ ቢቂላ ጤና ጣቢያ በግልጽ ጨረታ የተለያዩ ያገለገለ የቢሮ መገልገያ እቃዎችን እንዲሁም አልጋዎችን ባሉበት ሁኔታ አወዳድሮ በግልፅ ጨረታ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡

በአ/////5/ አበበ ቢቂላ ጤና ጣቢያ 4 ፎቅ ቢሮ ቁጥር 402 በመምጣት ለሽያጭ የተዘጋጁትን የተለያዩ ያገለገሉ የቢሮ መገልገያ እቃዎችን እንዲሁም አልጋዎችን ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ዘወትር በስራ ቀናት 230 እስከ 1100 ሰዓት ድረስ የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ:: በዚህም መሰረት ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለመጫረት የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የተጫራቾች መመሪያ የማክበርና የመፈፀም ግዴታ አለባቸው።

የጨረታ ሰነድ መሸጫ ዋጋ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር)

የተጫራቾች መመሪያ

  1. ተጫራቾች ለሽያጭ የተዘጋጁትን የተለያዩ ያገለገሉ የቢሮ መገልገያ እቃዎችን እንዲሁም አልጋዎችን ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 05 ተከታታይ የስራ ቀናት 230 እስከ 1100 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ የጨረታ ሰነዱን በመያዝ በጤና ጣቢያው ቅጥር ግቢ ውስጥ በአካል በመሄድ መመልከት ይችላሉ፣
  2. ተጫራቾች ከዚህ የጨረታ ሠነድ ጋር በተያያዘው የዋጋ ማቅረቢያ ቅጽ ላይ ስማቸውን፣ የሚኖሩበት ክፍለ ከተማ፣ወረዳ፣ የቤት ቁጥርና ስልክ ቁጥራቸውን (ተለዋጭ ስልክ ቁጥሮችን ጨምሮ) በመግለጽና በመፈረም ማቅረብ አለባቸው፡፡ በገዥው ወይም በሕጋዊ ወኪሉ ያልተፈረመ መጫረቻ ሰነድ ተቀባይነት የለውም፡፡
  3. ተጫራቾች በአንድ መለያ ቁጥር (መደብ) ስር ያለውን ንብረት ብዛት በሙሉ መጫረት አለባቸው፡፡
  4. ተጫራቾች በዋጋ ማቅረቢያ ቅጽ ላይ ተጫራቹ የሰጠው ዋጋ በሚለው አምድ ስር ንብረቱን የሚገዙበትን ዋጋ በአሃዝና በፊደል ስርዝ ድልዝ ሳይኖረው ጽፈው ከፈረሙ በኋላ በኤንቨሎፕ አሽገው የአ/////05 አበበ ቢቂላ ጤና ጣቢያ ቢሮ ቁጥር 402 ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ውስጥ ከጠዋቱ 230-1100 ሰዓት ድረስ ማስገባት አለባቸው፡፡
  5. ተጫራቹ በአሃዝ እና በፊደል በሰጠው ዋጋ ልዩነት ካለው አገልግሎቱ ከፍተኛውን ዋጋ በመውሰድ ያወዳድራል፡፡
  6. ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከጠዋቱ 400 ሰዓት ተዘግቶ በዚያኑ ቀን 430 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት 4 ፎቅ ቢሮ ቁጥር 402 ይከፈታል፡፡ ሆኖም ተጫራቾች በራሳቸው ምርጫ ጨረታው በሚከፈትበት ጊዜ ሳይገኙ በመቅረታቸው የጨረታውን መከፈት አያስተጓጉልም፡፡
  7. ከጨረታው መዝጊያ ሰዓት በኋላ የሚደርሱ የመጫረቻ ሰነዶች ተቀባይነት አይኖራቸውም፡፡
  8. ዋጋ ለመስበርና በተለያየ መንገድ ፍትሃዊ ውድድር እንዳይኖር በነጠላ ወይም በቡድን በሚመሳጠሩት ላይ አገልግሎቱ ተገቢውን ሕጋዊ እርምጃ ይወስዳል፡፡
  9. የጨረታው አሸናፊ የሚሆነው በጥቅል ለተመደቡት ዕቃዎች ከፍተኛ ዋጋ ያቀረበ ይሆናል፡፡
  10.  ተጫራቾች በጥቅል እኩል ዋጋ በመስጠት አሸናፊ ቢሆኑ እንደገና በማወዳደር አሸናፊው ይለያል፣ ድጋሚ ተመሳሳይ ዋጋ ከሰጡ አሸናፊው በእጣ እንዲለይ ይደረጋል፡፡ ነገር ግን ቀድሞ ከሰጡት ዋጋ በማሳነስ መዉዳደር ኢይቻልም፡፡
  11.  ተጫራቾች የሚጫረቱትን ንብረት በጥቅል ለተቀመጠው ጨረታ መነሻ ዋጋ 10 በመቶ (10%) የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ የኢ/////05 አበበ ቢቂላ ጤና ስም አሰርተው ከመጫረቻ ሰነዱ ጋር በማያያዝ ሣጥኑ ውስጥ ጨረታው ከመዘጋቱ በፊት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ የጨረታ ማስከበሪያው አሸናፊ ለሆኑት በሚከፍሉት ዋጋ ውስጥ ይታሰብላቸዋል። የሚዘጋጀው የጨረታ ማስከበሪያ /ሲፒኦ/ ከአዲስ አበባ ከተማ ውጭ ከሆነ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፎች ብቻ መሆን ይኖርበታል
  12.  አንድ ተጫራች ሌላው በሰጠው ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ አይችልም፡፡
  13.  ከጨረታ መነሻ ዋጋ በታች እና መነሻ ዋጋ ሞልቶ ያቀረበ ተጫራች ከጨረታው ይሰረዛል፡፡
  14.  ተጫራቾች ጨረታው ከተዘጋ በኋላ ከውድድሩ ሊወጡ አይችሉም፡፡
  15.  በጨረታው አሸናፊ የሆኑ ተጫራቾች አሸናፊነታቸው በተገለፀላቸው 7 የስራ ቀናት ውስጥ መክፈል ይኖርባቸዋል፡፡ ሆኖም ሙሉ ክፍያው በተጠቀሰው ጊዜ ገደብ መክፈል ካልቻሉ ያስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ ለአገልግሎት ገቢ ይደረጋል፡፡
  16.  አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፉበትን ገንዘብ አጠቃለው በመክፈል ዕቃዎቹን 5 የስራ ቀናት ውስጥ የማንሳት ግዴታ አለባቸው፡፡
  17.  ተጫራቾች በሚሰጡት ዋጋ ላይ የዋጋ ማስተካከያ ወይም ስርዝ ድልዝ ካደረጉ በተስተካከለው ፊት ለፊት መፈረም አለባቸው፡፡
  18.  የጨረታ ሰነዱን በስሙ ያልገዛ ተጫራች በጨረታው ሊሳተፍ አይችልም፤ ጨረታውን የሚካፈለው በወኪል ከሆነ ሕጋዊ የውክልና ማስረጃ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
  19.  የተሸጠ የጨረታ ሰነድ ተመላሽ አይደረግም፡፡
  20.  ፎቶ ኮፒ በተደረገ የጨረታ ሰነድ የተወዳደረ ተጫራች ከጨረታው እንዲሰረዝ ይደረጋል።
  21.  አንድ ተጫራች ለጨረታ ለቀረቡት ንብረቶች ከአንድ ጊዜ በላይ የጨረታ ሠነድ በማስገባት መወዳደር አይችልም፡፡
  • ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0118279062/01127332081 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
  • /ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

 

አበበ ቢቂላ ጤና ጣቢያ

 

Save Tender