የኢትዮጵያ ልማት ባንክ መነሻ ግምታቸው ብር 236,181.25 (ሁለት መቶ ሰላሳ ስድስት ሺህ አንድ መቶ ሰማንያ አንድ ብር ከ75/100 ሳንቲም) የተለያየ መጠን ያላቸው ያገለገሉ ፐርኪ ጣውላዎች ባሉበት ሁኔታ በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
ያገለገሉ የጣሪያ ኮርኒስ ፐርኬ ጣውሳ ሽያጭ
ጨረታ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ መነሻ ግምታቸው ብር 236,181.25 (ሁለት መቶ ሰላሳ ስድስት ሺህ አንድ መቶ ሰማንያ አንድ ብር ከ75/100 ሳንቲም) የተለያየ መጠን ያላቸው ያገለገሉ ፐርኪ ጣውላዎች ባሉበት ሁኔታ በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
- ተጫራቾች የሚገዙበትን ዋጋ በመጥቀስና የታደሰ የነዋሪነት መታወቂያ በማያያዝ በሰም በታሸገ ኤንቨሎኘ በማድረግ ይህ ማስታወቂያ ከወጣ ከሶስተኛው ቀን ጀምሮ በኢትዮጵያ ልማት ባንክ ምድር ቤት ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ እስከ ግንቦት 25 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይችላሉ፡፡
- የጨረታ ሳጥኑ ግንቦት 25 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ታሽጐ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ግንቦት 25 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:05 ይከፈታል፡፡
- በጨረታው መሳተፍ የሚፈልግ በቅድሚያ ለጨረታ ማስከበሪያ የሚሆን የመነሻ ዋጋውን 25% (ሃያ አምስት በመቶ) በገንዘብ የክፍያ ማዘዣ /ሲፒኦ/ ጨረታው በሚከፈትበት ዕለት ይዞ መቅረብ አለበት።
- አሸናፊው ለጨረታ ማስከበሪያነት በሲፒኦ ያስያዘው ገንዘብ ከግዢው ዋጋ ጋር ሲታሰብለት ለተሸነፉት ያስያዙት ገንዘብ ወዲያውኑ ይመለስላቸዋል፡፡
- ተጫራች ሁሉንም ፐርኬ ጣውላ ባሉበት ሁኔታ አጠቃለው የሚገዛ ድርጅት/ግለሰብ መሆን ይችላል።
- የጨረታው አሸናፊ ማሸነፉ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር 10 ተከታታይ ቀናት የገዛበትን ገንዘብ ሙሉ በሙሉ ከፍሎ ጣውላዎቹን መረከብ ይኖርበታል፡፡ ይህ ካልሆነ ጨረታው ተሰርዞ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዘው ገንዘብ ሙሉ ለሙሉ ለባንኩ ገቢ ይሆናል፡፡
- የጨረታው አሸናፊ /ገዥው/ በገዛበት ዋጋ ላይ የተጨማሪ እሴት ታከስ 15% /አስራ አምስት በመቶ/ መክፈል ይጠበቅበታል፡፡
- ስለ ንብረቱ ተጨማሪ መረጃ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ዋና መ/ቤት በስልክ ቁጥር 0115511188/89 በቀጥታ መስመር ደውሎ ማግኘት ይቻላል፡፡
- ተጫራቾች እነዚህን ያገለገሉ ፐርኬ ጣውላዎች መመልከት ከፈለጉ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ዋና መ/ቤት ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት በአካል በመገኘት መመልከት ይችላሉ፡፡
- ባንኩ ካገለገሉ ፐርኬ ጣውላ አሻሻጥ ጋር በተያያዘ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በመሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
