በኢፌዲሪ ጉምሩክ ኮሚሽን የጋላፊ ጉምሩከ ቅ/ጽ/ቤት ኮስሞቲክስ፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ ስፔር ፓርት እና ልዩ ልዩ ዕቃዎች በሀራጅ ጨረታ ሽያጭ ማስታወቂያ ጨ.ቁ 43/2017 ዓ.ም እቃዎቹን ባሉበት ሁኔታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
በኢፌዲሪ ጉምሩክ ኮሚሽን የጋላፊ ጉምሩከ ቅ/ጽ/ቤት ኮስሞቲክስ፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ ስፔር ፓርት እና ልዩ ልዩ ዕቃዎች በሀራጅ ጨረታ ሽያጭ ማስታወቂያ ጨ.ቁ 43/2017 ዓ.ም እቃዎቹን ባሉበት ሁኔታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም:-
- በጨረታው ሽያጭ ስርዓት ለመወዳደር የሚፈልግ ተጫራች በዘርፉ የጸና የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፊኬት፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና የዘመኑን ግብር የከፈሉ ስለመሆኑ ከግብር ሰብሳቢ መስሪያ ቤት የተሰጠ ማስረጃ በጨረታ መክፈቻ ቀን ይዘው መቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ዘወትር በስራ ሰዓት ከሰኞ እስከ አርብ እና ቅዳሜ ጠዋት ከ2፡00-6፡00 ሰዓት የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በመገኘት ይህ ጨረታ አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ በውርስ መጋዘን አስተዳደር የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 08 በመምጣት መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ለሚወዳደሩባቸው ዕቃዎች ለእያንዳንዳቸው 100,000 (አንድ መቶ ሺህ) ብር ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (CPO) በጋላፊ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት ስም በባንክ አሰርተው ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች በሚከተለው የጨረታ የጊዜ ሰሌዳ (ስኬጁል) መሠረት መጫረት ይችላሉ፡፡
|
ተ.ቁ |
የቅ/ጽ/ቤቱ ስም |
የጨረታው አይነት |
የንብረት መመልከቻ ቀን የጨረታው ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ |
የጨረታው መክፈቻ ቀንና ሰዓት |
|
2 |
ጋላፊ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት |
ሀራጅ ጨረታ |
እስከ 05/09/2027 |
05/09/2017 ዓ.ም 3፡30 ሰዓት ይከፈታል |
- የጨረታው መክፈቻ ቦታ ፡- በጋላፊ ጉ/ቅ/ጽ/ቤት የሚካሄድ ሲሆን ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በሚገኙበት ይከፈታል፡፡ተጫራቾች በተራ ቁጥር አንድ የተጠቀሱ ማስረጃዎች ኦሪጅናል ይዘው መቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች ያስያዙትን ዋስትና (CPO) በተመለከተ ለአሸናፊው ተጫራች ካሸነፉት የዕቃ ዋጋ ላይ የሚታሰብላቸው ሲሆን ለተሸናፊ ተጫራቾች የጨረታ ውጤቱ በተገለጸ በ3 (ሶስት) ቀናት ውስጥ ተመላሽ ይደረግላቸዋል፡፡
- አሸናፊ ተጫራች ማሸነፋቸውን በደብዳቤ ከተገለጸላቸው ቀን ጀምሮ በ05 (በአምስት) ቀናት ውስጥ ያሸነፉበትን እቃ ዋጋ ገቢ በማድረግ እቃውን መረከብ ያለበት ሲሆን ይህን ባይፈጽም ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ዋስትና ለመስሪያ ቤቱ ገቢ ተደርጎ ዕቃው በድጋሚ ለጨረታ የሚቀርብ ሲሆን ነገር ግን የእቃውን ዋጋ ገቢ አድርጎ በተቀመጠው ጊዜ ውስጥ እቃውን ያላነሳ እንደሆነ ለሚቆይበት ተጨማሪ ጊዜ የመጋዘን ኪራይ የሚከፍል ይሆናል፡፡ ሆኖም እቃውን በሁለት ወር ውስጥ ካላወጣ ለንብረቱ የተከፈለው ዋጋ ለመስሪያ ቤቱ ገቢ ሆኖ እቃው እንደተተወ ተቆጥሮ በሽያጭ ይወገዳል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ በስ/ቁ፡- 0335590114 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
ጋላፊ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት
