መ/ቤታችን የሂሣብ ምርመራ አገልግሎት ኮርፖሬሽን 10 ፕሪንተር ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ብሔራዊ ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር ሂምአኮ/007/2017
መ/ቤታችን የሂሣብ ምርመራ አገልግሎት ኮርፖሬሽን ከዚህ በታች የተመለከተውን ንብረት ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
10 ፕሪንተር፣
በመሆኑም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ የፕሪንተር አቅራቢ ድርጅቶች እንዲወዳደሩ እየጋበዝን፤ ተጫራቾች ከሚያቀርቡት የጨረታ ሰነድ ጋር አካተው ማቅረብ ያለባቸው ሰነዶች
- በዘርፉ ህጋዊ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸውና ለዘመኑ የታደሰበት ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ፤
- ማንኛውንም የወቅቱን የመንግስት ገቢ ግብር ለመክፈላቸው ወይም ሌሎች ግዴታዎችን ለመወጣታቸው ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ፤
- በመንግስት ጨረታዎች መሳተፍ የሚያስችል ማረጋገጫ የምዝገባ ምስክር ወረቀት አግባብ ካለው ሕጋዊ አካል ማቅረብ የሚችሉ፤
- ተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይ ለመሆናቸው የሚያረጋግጥ የምዝገባ የምስክር ወረቀት አግባብ ካለው ሕጋዊ አካል ማቅረብ የሚችል፤
- የጨረታ ማስከበሪያ በኮርፖሬሽኑ ስም (Audit Service Corporation) የተዘጋጀ ብር 50,000 /ሃምሳ ሺህ ብር/ በሲፒኦ ብቻ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፤
- ተጫራቾች የቴክኒካልና ፋይናንሽያል ፕሮፖዛላቸውን ለየብቻ በታሸገ ኢንቨሎፕ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፤
- ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ቅዳሜና እሁድን ሳይጨምር በኮርፖሬሽኑ የሥራ ሰዓት ለአስር ተከታታይ የሥራ ቀናት ክፍት ሆኖ ስለሚቆይ ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ የማይመለስ ብር 100 /አንድ መቶ/ በመክፈል 7ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 712 መውሰድ ይችላሉ።
- ጨረታው በ11ኛው የሥራ ቀን ላይ ከጠዋቱ በ4፡00 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይታሸጋል፡፡ በዕለቱ በ5፡00 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የጨረታው ሰነድ ይከፈታል፡፡
- ኮርፖሬሽኑ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ይሁን ሙሉ በሙሉ የመቀበልም ሆነ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
አድራሻ፡- ካዛንቺስ ከሲንቄ ባንክ ፊት ለፊት ያለው ህንፃ
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0913 16 65 04/ 0911 43 88 49/ 0922 87 86 63
የሂሣብ ምርመራ አገልግሎት ኮርፖሬሽን
