ጉዳ ትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ አ.ማ የተለያዩ ያገለገሉ የተሸከርካሪ ጎማዎች የተቃጠሉ ዘይቶች እና እስከራፕ ባሌስትራዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
የሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታው ቁጥር [Gada/NCB/09/2017]
ጉዳ ትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ አ.ማ የተለያዩ ያገለገሉ የተሸከርካሪ ጎማዎች የተቃጠሉ ዘይቶች እና እስከራፕ ባሌስትራዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም በጨረታው መወዳደር የምትፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተመለከቱትን መስፈርቶች በሟሟላት መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን ፡፡
- ኢትዮጵያዊ የሆነ/የሆነች እና የታደሰ የነዋሪነት መታወቂያ ያለው ወይም ያላት እና በማንኛውም ንግድ ስራ ላይ የተሰማራ ወይም የተሰማራች
- ማንኛውም ተወዳዳሪ ተጫራች የጨረታ ሰነድ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 16 ቀን እየር ላይ የሚውል ሲሆን ሰንጋ ተራ ንግድ ስራ ኮሌጅ ፊት ለፊት ቢፍቱ አዱኛ ህንጻ 12ኛ ፎቅ ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 1፡00 ሰዓት በመምጣት የማይመለስ 100 (አንድ መቶ) ብር በመክፍል የጨረታ ሰነዱን በመግዛት መወዳደር ይችላሉ፡፡
- ማንኛውም ተጫራች በገዛው የጨረታ ሰነድ ላይ ከብ ማህተም ወይም በመፈርም በሰም በታሸገ ፖስታ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ አጠቃላይ ከተወዳደሩበትን ዋጋ 2% በ ሲ.ፒ.ኦ ማቅረብ ያለባቸው ሲሆን የሞሉትን ጨረታ እንዲሁም ያስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በአንድ ላይ በፖስታ በማሸግ ማቅረብ አለባቸው።
- የጨረታ ሰነድ የገዙ ተወዳዳሪዎች የገዙትን ሰነድ እና ደረሰኝ በመያዝ እቃዎችን ሞጆ በሚገኘው የድርጅቱ የተሽከርካሪ ማቆሚያ ግቢ ውስጥ ማየት ይቻላል።
- የጨረታ አሸናፊነቱ ከተረጋገጠ ቀን ጀምሮ ባሉት 5 ተከታታይ የስራ ቀናት አጠቃላይ ያሸነፉበትን እቃ ሙሉ በሙሉ በመክፈል እቃውን ከጊቢ ማውጣት አለባቸው፡፡
- ተጫራች በሚያቀርቡት ዋጋ የጨረታ መግቢያ ሰዓት ከተጠናቀቀ በኋላ ማሻሸያ ማድረግ እና እራሳቸውን ከጨረታ ማግለል አይቻልም።
- ጨረታው የሚከፈትበት ቀን የጨረታ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 16 ቀን አየር ላይ የሚውል ሆኖ በ16ኛው ቀን በ8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዛው እለት 8፡30 ላይ ተጫራቾች እና ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የሚከፈት ይሆናል፡፡
- ንብረቶቹ የሚገኙበት ቦታ ሞጆ ይገኛሉ።
- የጨረታ መክፈቻ ቀናት ፤ ቅዳሜ እና እሁድ እንዲሁም በበዓላት ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት የሚከፈት ይሆናል፡፡
- ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ - ሰንጋ ተራ ንግድ ስራ ኮልጅ ፊት ለፊት ቢፍቱ አዱኛ ህንጻ 12ኛ ፎቅ ለበለጠ መረጃ
ስልክ ቁጥር 011-558-25-19
ገዳ ትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ አ.ማ
