የፈደ/ማረ/ቤት ኮሚሽን ንብረትነታቸው የኮሚሽኑ የሆነና በተለያዩ ማእከላት ተከማችተው የሚገኙ ቁርጥራጭ ብረታ ብረትና የብረታ ብረት ውጤቶችን ባሉበት ሁኔታ ከፈዴራል የገንዘብ ሚ/ር የተሰጠ የመነሻ ዋጋን መሠረት በማድረግ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
ቁርጥራጭ ብረታ ብረቶችን በጨረታ ለመሸጥ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
የፈደ/ማረ/ቤት ኮሚሽን ንብረትነታቸው የኮሚሽኑ የሆነና በተለያዩ ማእከላት ተከማችተው የሚገኙ ቁርጥራጭ ብረታ ብረትና የብረታ ብረት ውጤቶችን ባሉበት ሁኔታ ከፈዴራል የገንዘብ ሚ/ር የተሰጠ የመነሻ ዋጋን መሠረት በማድረግ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
ስለሆነም ተጫራቾች ከዚህ በታች የተመለከቱትን መስፈርቶች በማሟላት ቀርበው መወዳደር ይችላሉ ፡፡
- በጨረታው ላይ የሚወዳደሩት በማእድን ሚ/ር የተለዩ ብረት አቅላጭ የግል ድርጅት የሆኑና የጨረታውን ሰነድ ለመግዛት ሲመጡ ይህንኑ የሚያረጋግጥ ማስረጃ እና መታወቂያ ማቅረብ የሚችሉ ናቸው።
- ተጫራቾች ፒያሳ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አጠገብ በሚገኘው የፌዴራል ማረ/ቤት ኮሚሽን 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 407 ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት በመምጣት የብረቶቹን ዝርዝር መረጃ፣ የተጫራቾች መመሪያና የዋጋ ማቅረቢያ ቅፅ የያዘ ሰነድ የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) በመክፈል የጨረታውን ሰነድ ከቢሮ ቁጥር 105 መውሰድ ይችላሉ።
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ከገዝዙ በኋላ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ቀናት ከጠዋቱ 2:30 ሰዓት እስከ 11፡00 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ ብረታ ብረቶቹን ከፍተኛ ጥበቃ ማረ/ማእከል (ገላን) ዝዋይ ተኋ/ልማት ማረ/ማእከል ፣ ድሬዳዋ ሁሉ አቀፍ ማረ/ማረ/ማዕከልና ማረ/ፖሊስ ማሰ/ተቋም (አሌልቱ) መሆኑን ተገንዝባችሁ ንብረቶቹ ያሉበትን ሁኔታ በአካል ተገኝቶ መመልከት የሚቻል ሲሆን ለምልከታው ቀድማችሁ ፕሮግራም በማስያዝ የንብረቶቹን ይዞታ ማየት የምትችሉ መሆኑን ከወዲሁ እናስገነዝባለን፡፡
- ተጫራቾች ለሚወዳደሩበት ለእያንዳንዱ ቁርጥራጭ የብረት ዓይነት የጨረታ መነሻ 10% (አስር በመቶ) የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ከጨረታ ሰነዱ ጋር በማያያዝ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ከመዝጊያው ሰዓት በፊት ማስገባት አለባቸው።
- የሚዘጋጀው የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ (CPO) ከአዲስ አበባ ከተማ ውጭ ከሆነ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፎች የተዘጋጀ መሆን አለበት።
- የጨረታው መገምገሚያ መስፈርት ዋጋ፣ የተሟላ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ሲፒኦ (CPO) እንዲሁም በሰነዱ የተገለፁትን አሟልቶ መገኘት ይኖርበታል። ይሁን እንጂ የብረታ ብረቶቹን ግምታዊ ጠቅላላ ዋጋ 10% (አስር በመቶ) ዋስትና ያሳስያዘ እንዲሁም በሰነዱ ውስጥ የተጠቀሱ ሌሎች ነጥቦችን ያላሟላ ተጫራች ከጨረታው ውድቅ ይደረጋል።
- የጨረታ ማስገቢያ ሣጥኑ ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛው ቀን ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ እለት ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በኮሚሽኑ የግዥ/ን/አስተ/ዳይሬከቶሬት ቢሮ ቁጥር 407 ይከፈታል። ነገር ግን በጨረታው መክፈቻ ቀን ኮሚሽኑን ከአቅም በላይ የሆነ ጉዳይ ከገጠመው ቀጥሎ ባለው የስራ ቀን ጨረታው እንዲከፈት ይደረጋል። ቅዳሜና እሁድ እንዲሁም በብሔራዊ በዓል ቀን የጨረታ ስነ-ስርዓት አይኖርም። ይሁንና ተጫራቾች በራሳቸው ምርጫ ጨረታው በሚከፈትበት እለት ሳይገኙ ቢቀሩ የጨረታውን አከፋፈት ስነስርዓት እያስቀረውም።
- ጨረታውን አሸናፊ የሆኑ ተጫራቾች አሸናፈነታቸው ከተገለፀላቸው 7 (ሰባት) የስራ ቀናት በኋላ በ5 (አምስት) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ያሸነፉበትን ዋጋ ሙሉ ክፍያ ማጠናቀቀ ይኖርባቸዋል። ይሁንና ሙሉ ክፍያውን በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ውስጥ መክፈል ካልቻሉ ያስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ውርስ ተደርጎ ለመንግስት ገቢ እንዲሆን ይደረጋል።
- ጨረታውን አሸናፈ የሆኑ ተጫራቾች ያሸነፈባቸውን ብረታ ብረቶች ሙሉ ክፍያ ፈፅመው እስከሚወስዱ ድረስ ለውል አተገባበር ዋስትና የሚሆን የጠቅላላ ዋጋውን 10% (አስር በመቶ) በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ማስያዝ አለባቸው።
- ተጫራቾች ያሸነፉትን ቁርጥራጭ ብረታ ብረት በራሳቸው ወጪ በማጓጓዝ የሚዛንና ሌሎች ወጪዎችን በመሸፈን ብረታ ብረቱ ከሚገኝበት ስፍራ ቅርብ በሆነ የመንግስት የምድር ሚዛን በማስመዘን ፕሪንት አውት በማቅረብ ውል በፈረሙ በ15 (አስራ አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ ቁርጥራጭ ብረታብረቶቹን በማንሳት ማጠናቀቅ አለባቸው። ግምታዊ መጠኑ ከፕሪንት አውት ከሚገኘው ትክክለኛ የብረቱ መጠን ጋር የሚኖረው ልዩነት ታስቦ አሸናፊው ተጫራች ተጨማሪ ክፍያ የሚኖርበት ከሆነ የውል ጊዜው ከመጠናቀቁ በፊት የሚኖረውን ልዩነት ሂሳብ መክፈል ያለበት ሲሆን ገዥው በትርፍ የሰጠው ገንዘብ ካለ በኮሚሽኑ ተመላሽ ይደረጋል።
- ኮሚሽኑ ያመጣውን የጨረታ ሰነድ በስሙ ሳይገባ የተወዳደረ ማንኛውም ተጫራች ከውድድሩ ውጭ ይደረጋል፡፡
- አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፉበትን ገንዘብ አጠቃለው በመክፈል ንብረቶቹን በ15 (አስራ አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ የማንሳት ግዴታ አለባቸው፡፡
- ኮሚሽኑ የተሻለ አማራጭ ወይም ሌላ ጨረታውን ለመሰረዝ የሚያበቃ ምክንያት ካጋጠመው ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ :- ፒያሳ ፌዴራል ማረ/ቤት ኮሚሽን ዋ/መ/ቤት ከአዲስ-አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከፍ ብሎ ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 011-1-26-54-80/09-23-27-37-67/09-11-05-20-26 ደውሎ መጠየቅ ይችላል።
የፌዴራል ማረ/ቤት ኮሚሽን
አዲስ አበባ
