ድርጅታችን ኬኬ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ አቃቂ ጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ የግንባታ ተረፈ ምርቶች ያገለገሉ የመኪና ዕቃዎች፤ የፋብሪካ ተረፈ ምርቶች እንዲሁም ሌሎች ንብረቶችን በግልፅ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
ኬኬ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
ድርጅታችን ኬኬ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ አቃቂ ጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ የግንባታ ተረፈ ምርቶች ያገለገሉ የመኪና ዕቃዎች፤ የፋብሪካ ተረፈ ምርቶች እንዲሁም ሌሎች ንብረቶችን በግልፅ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል። በዚህም ጨረታ ላይ ለመወዳደር የምትፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች ያለውን መስፈርት በማሟላት መወዳደር የምትችሉ መሆኑንን ያሳውቃል።
- ተጫራቾች ዘወትር በስራ ቀናት ከግንቦት 13/2017 እስከ ግንቦት 25/2017 ከ2:30 እስከ 10፡00 ሰዓት ፋብሪካ በመሄድ ለጨረታ የወጡትን ንብረቶች መመልከት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት በፋብሪካችን የማይመለስ ብር 500 (አምስት መቶ ብር) ከፍለው የጨረታ ዝርዝር ሰነድ መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች ለማወዳደር ያቀረቡትን ጠቅላላ ዋጋ 10% (አስር በመቶ) የጨረታ ማስከበሪያ በሲፒኦ ገቢ ያደርጋሉ።
- የጨረታው ሳጥን ግንቦት 25/2017 ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚያኑ ቀን በ4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ግንቦት 25/2017 በተረፈ ምርት ጨረታ ሽያጭ ኮሚቴ ይከፈታል።
- ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ ተጫራቾች የሚከተለውን አድራሻ መጠቀም ይችላሉ።
አድራሻ -- አቃቂ ቃሊቲ ከስቴድየም በታች ሰላም ህንፃ ፊት ለፊት ስልክ ቁጥር 0115 15 90 15
