የጉምሩክ ኮሚሽን አዲስ አበባ ኤርፖርት ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት ስማድል ኮሚውኒኬሽን ተርሚናል ፋብሪካ ኃላ/የተ/የግ/ማህበር ለአለበት ዕዳ በታክስ ህጉ በተፈቀደው የጊዜ ገደብ ባለመክፈላቸው ምክንያት በታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 አንቀፅ 41 በተሠጠው ስልጣን መሰረት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 05 አክሰስ ሪል እስቴት እና እሳት አደጋ መከላከያ መካከል የሚገኝ የይዞታ ልዩ መለያ ቁጥር AA000060502305 የሆነ G+4 መኖሪያ ቤት ባለበት ሁኔታ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የጉምሩክ ኮሚሽን አዲስ አበባ ኤርፖርት ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት በታክስ ዕዳ የያዘውን መኖሪያ ቤት ለመሸጥ የወጣ የግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ መ/ቤት ቁጥር 1/2017 ቅ/ጽ/ቤቱ ስማድል ኮሚውኒኬሽን ተርሚናል ፋብሪካ ኃላ/የተ/የግ/ማህበር ለአለበት ዕዳ በታክስ ህጉ በተፈቀደው የጊዜ ገደብ ባለመክፈላቸው ምክንያት በታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 አንቀፅ 41 በተሠጠው ስልጣን መሰረት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 05 አክሰስ ሪል እስቴት እና እሳት አደጋ መከላከያ መካከል የሚገኝ የይዞታ ልዩ መለያ ቁጥር AA000060502305 የሆነ G+4 መኖሪያ ቤት ባለበት ሁኔታ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
በመሆኑም፡-
- በግልፅ ጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች ማንነቱን የሚገልፅ የነዋሪነት መታወቂያ (ፓስፖርት) ኮፒ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዞ በኤንቨሎፕ በማሸግ ለግልፅ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርበታል።
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ይህ የግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት ከሰኞ እስከ አርብ እና ቅዳሜ ጠዋት ከ2፡00-6፡00 ሰዓት አዲስ አበባ ኤርፖርት ጉምሩከ ቅ/ጽ/ቤት ገርጂ ጉምሩክ መጋዘን አስተዳደር ቅጥር ግቢ የውርስ ዕቃዎች አወጋገድ ቡድን ቢሮ መውሰድ ይኖርበታል።
- በግልፅ ጨረታ ለመሳተፍ ተጫራቾች ለሚወዳደሩበት ቤት የሰጡትን ዋጋ 1/10ኛውን ብቻ ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (CPO) "በጉምሩክ ኮሚሽን አ/አ/ኤርፖርት ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት" (CUSTOMS COMMISSION ADDIS ABABA AIRPORT CUSTOMS BRANCH OFFICE) ስም በባንክ አሰርተው ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች በሚከተለው ጨረታ ቀናት (ስኬጁል)መሰረት ስነድ ገዝተው መጫረት ይችላሉ፡
|
ተ.ቁ |
የመ/ቤቱ ስም |
ለጨረታ የቀረበው የንብረት ዓይነት |
የንብረቶቹ መመልከቻ ቀን |
የጨረታው የመዝጊያ እና የመክፈቻ ቀን |
|
1
|
አዲስ አበባ ኤርፖርት ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት |
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቦሌ ክ/ ከተማ ወረዳ 05 የይዞታ ልዩ መለያ ቁጥር AA000060502305 የሆነ G+4 መኖሪያ ቤት |
ማስታወቂያው አዲስ ዘመን በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ30 ቀናት |
ማስታወቂያው በጋዜጣ ወጥቶ 30 ቀን ከተጠናቀ በኋላ ቀጥሎ ባለው የስራ ቀን 8:00 ሰዓት ተዘግቶ በዚያኑ ቀን በ8፡15 ሰዓት ይከፈታል |
- የጨረታ መክፈቻ ቦታ ገርጂ ጉምሩክ መጋዘን አስተዳደር ቅጥር ግቢ የጨረታ አዳራሽ/ የሰራተኞች ካፈ ተጫራቾች ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት ወይም በታዛቢዎች ፊት ይከፈታል።
- የግልፅ ጨረታው መክፈቻና መዝጊያ ማስታወቂያው በጋዜጣ ወጥቶ 30 ቀን ከተጠናቀ በኋላ ቀጥሎ ባለው የስራ ቀን የመ/ቤቱ የሥራ ቀን ካልሆነ በቀጣዩ የስራ ቀን የግልፅ ጨረታው መክፈቻና መዝጊያ ቀን ይሆናል።
- ለጨረታው አሸናፊ ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ያስዙት (CPO) ከሚከፍሉት ዋጋ ጋር እንደ አስፈላጊነቱ የሚታሰብላቸው ሲሆን ለተሸናፊ ተጫራቾች ደግሞ የግልፅ ጨረታ ኮሚቴው መረጃውን አጣርቶ እንደጨረሰ በ5 የስራ ቀናት ውስጥ ተመላሽ ይደረግላቸዋል።
- የቤት ጨረታ ለሚያሸንፉ ተጫራቾች ከስመ-ንብረት ዝውውር ጋር ተያያዥነት ያላቸውን ወጪዎች ሻጭን አይመለከትም።
- አሸናፊ ተጫራቾች ማሸነፋቸው በደብዳቤ ከተገለፀላቸው ቀን ጀምሮ ባሉት 30 ቀናት ውስጥ ያሸነፉበትን ጠቅላላ ዋጋ መ/ቤቱ በሚሠጠው አድራሻ ገቢ በማድረግ ያሸነፉበትን ሀብት ንብረት መረከብ ይኖርባቸውል።
- ከላይ በተ/ቁ.9 በተገለጹት ቀናት ውስጥ ክፍያውን ገቢ በማድረግ ንብረታቸውን ያልተረከቡ ተጫራቾች የግልፅ ጨረታው ተሰርዞ ለጨረታ ማስከበሪያ በCPO ያስያዙት የዋስትና ገንዘብ ለቅ/ጽ/ቤቱ ግቢ ሆኖ ንብረቱ እንዳልተሸጠ ተቆጥሮ በቀጣይ በድጋሚ ለሽያጭ ይቀርባል።
- ቅ/ጽ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ የግልፅ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ፣ አ/አ/ኤ/ፖ/ጉ/ቅ/ጽ/ቤት በስልክ ቁጥር 011-668_4537 እና 011-668 4193 ደውለው መጠየቅ ይቻላል።
በኢትዮጵያ ፊዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የጉምሩክ ኮሚሽን አዲስ አበባ ኤርፖርት ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት
