ገነት ሆቴል በግቢው ውስጥ ያለውን የመጠጥ ጉርጓድ ውሃ ጥገና ስራ ለማሰራት ብቁ የሆኑ የሃገር በቀል በጉርጓድ ውሃ ስራ ተቋራጭነት ደረጃ-5 (አምስት) እና ከዚያ በላይ የሆኑትን ድርጅቶችን በግልፅ ጨረታ በማወዳደር ማሰራት ይፈልጋል፡፡
መጠጥ ጉርጓድ ውሃ ጥገና ስራ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
ገነት ሆቴል በግቢው ውስጥ ያለውን የመጠጥ ጉርጓድ ውሃ ጥገና ስራ ለማሰራት ብቁ የሆኑ የሃገር በቀል በጉርጓድ ውሃ ስራ ተቋራጭነት ደረጃ-5 (አምስት) እና ከዚያ በላይ የሆኑትን ድርጅቶችን በግልፅ ጨረታ በማወዳደር ማሰራት ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች እንዲሁም የሰው ኃይል፤ ማሽን በማሟላት የሚችሉ ስራ ተቋራጮች ስራውን ለማከናወን በግልፅ ጨረታ ውድድር መሳተፍ ይችላሉ፡፡
- የ2017 ዓ.ም ዘመን የታደሰ የንግድ ፍቃድ ማቅረብ የሚችሉ፤
- በጉርጓድ ውሃ ስራ ደረጃ -5 (አምስት) ብቃት ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችል፤
- የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ ሰርተፍኬት (VAT) ያላቸው፤
- የግብር ከፋይ ምዝገባና ሰርተፍኬትና መለያ ቁጥር (TIN) ሰነድ ያላቸው፤
- በጨረታ ለመሳተፍ የታክስ ክሊራንስ ማስረጃ ያላቸው ፤
- ተጫራቾች ስለጨረታው ሙሉ ዝርዝር ሁኔታ የያዘውን የጨረታ ሰነድ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ታሳቢ የሚደረግ 15 (አስራ አምስት) ተከታታይ ቀናት ጊዜ ውስጥ ከድርጅታችን የፋይናስ ቢሮ ክፍል የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ 500.00 (አምስት መቶ ብር) ከፍለው መውሰድ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 30,000.00 (ሰላሳ ሺህ ብር) በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና "ለገነት ሆቴል" በሚል በማሰራት ከቴክኒካል ሰነድ ጋር ለብቻው በፖስታ በማሸግ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የቴክኒካል ሰነድ እና ስራውን የመስሪያ ፋይናንሻል ሰነድ ለእያንዳቸው አንድ ኮፒ በማዘጋጀት በተናጥል ለየብቻ በማሸግ በጥቅል በአንድ በሰም በታሸገ ፖስታ በማደረግ እስከ በአስራ አምስተኛ (15) ቀን ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ በድርጅቱ የፍይናስ ክፍል ቢሮ ለዚሁ አገልግሎት በተዘጋጀው ሳጥን ማስገባት ይጠበቅባቸዋል ፡፡ አስራ አምስተኛ ቀን የስራ ቀን ካልሆነ የጨረታው መክፈቻ በቀጣይ ባለው ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይሆናል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ተወካዮች ባሉበት በአስራ አምስተኛ (15) ከቀኑ 8፡30 በድርጅቱ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
- ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አደራሻ፡- አ/አ ከሜክሲኮ ወደ ቄራ በሚወስደው መንገደ ላይ ገነት ሆቴል ግቢ ውስጥ
ለተጨማሪ ማብራሪያ፦ +251-0115-51-47-70/+251-115-50-47-01/0911-250641
ገነት ሆቴል
