በወሎ ዩኒቨርሲቲ የላኮመንዛ ንግድና የማማከር ስራዎች ኢንተርፕራይዝ በስሩ ለሚገኘው መድሃኒት ቤት አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ የሰው መድሃኒቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 009/2017
በወሎ ዩኒቨርሲቲ የላኮመንዛ ንግድና የማማከር ስራዎች ኢንተርፕራይዝ በስሩ ለሚገኘው መድሃኒት ቤት አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ የሰው መድሃኒቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም፡-
- ተጫራቾች - የዘመኑን ግብር የከፈሉ በዘርፉ አግባብ ያለውና የታደሰ ንግድ ፈቃድ፡ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት፡ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር /ቲን/ ፡ የታክስ ክሊራንስ፡ የአቅራቢነት ምዝገባ ምስክር ወረቀት ተያያዥ ማስረጃዎችን ማቅረብ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ የሚሆን በኢትዮጵያ በታወቀ ባንክ የተመሰከረለት የብር 25,000.00 (ሃያ አምስት ሺህ) CPO በድርጅቱ ትክክለኛ ስም ላኮመንዛ ንግድና የማማከር ስራዎች ኢንተርፕራይዝ በማሰራት ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ መግዣ የማይመለስ ብር 200.00 (ሁለት መቶ) በመክፈል ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 16ኛው ቀን ዘወትር በሥራ ሰዓት ከኢንተርፕራይዙ አስ/ፋይ/አገ ዘርፍ ግዥ ቡድን ቢሮ መግዛት ይችላሉ።
- ጨረታውን የሚያቀርበውና የሚፈርመው ወኪል ከሆነ ከሚመለከተው ውክልና ሰጪ (መዝጋቢ አካል) የተሰጠ ህጋዊ የውክልና ማስርጃ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
- ተጫራቾች የሚያቀርቡትን ዕቃ ነጠላና ጠቅላላ ዋጋ በጨረታ ሰነዱ በመሙላት ዋናና አንድ ኮፒ በታሸገ ፖስታ የተጫራቹ ድርጅት ማህተም ተደርጎበትና ተፈርሞ ወሎ ዩኒቨርሲቲ ደሴ ካምፓስ ብሎክ 20 ቢሮ ቁጥር 2023 በሚገኘው የኢንተርፕራይዙ አስ/ፋይ/እገ ዘርፍ ግዥ ቡድን ቢሮ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ ማስገባት አለባቸው፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከላይ በተራ ቁጥር 5 በተጠቀሰው ቀን እና ቢሮ ከጠዋቱ 4፡30 በግልፅ ይከፈታል፣ ቀኑ የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይከፈታል።
- ተጫራቾች ባይገኙም ሰነዳቸው የተሟላ ሆኖ ከተገኘ በሌሉበት የሚከፈት ይሆናል፡፡
- ከተጠቀሰው ሰዓት ዘግይቶ የሚመጣ የመወዳደሪያ ሃሳብ ወይም ጨረታ ሰነዶች ተቀባይነት የላቸውም ተጫራቾች አሸናፊ ከሆኑ ያሸነፉበትን ዕቃ የኢንተርፕራይዙ ንብረት ክፍል የሚገኝበት ወሎ ዩኒቨርሲቲ ደሴ ካምፓስ ድረስ በማቅረብ ማስረከብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች አሸናፊ ከሆኑ ላሸነፉበት ጠቅላላ ዋጋ 10% በኢትዮጵያ በታወቀ ባንክ የተመሰከረለት CPO ውል ማስከበሪያ በቅድሚያ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- አሸናፊ ተጫራች በውሉ ውስጥ የተካተቱትን ህጐች ማክበር አለባቸው፡፡
- ኢንተርፕራይዙ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0970750336 መጠቀም ይችላል
የላኮመንዛ ንግድና የማማከር ስራዎች ኢንተርፕራይዝ
