ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥር ድርጅት ለቢሮ አገልግሎት የሚውሉ ኤሌክትሮኒክሶች (ኮምፒውተር፣ ፕሪንተር ፣ ፎቶ ኮፒ ማሽን እና ፕሮጀክተር) በሀገር አቀፍ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ በማውጣት አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ መለያ ቁጥር NCB 0001/2017
ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥር ድርጅት ለቢሮ አገልግሎት የሚውሉ ኤሌክትሮኒክሶች (ኮምፒውተር፣ ፕሪንተር ፣ ፎቶ ኮፒ ማሽን እና ፕሮጀክተር) በሀገር አቀፍ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ በማውጣት አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
በዚሁ መሰረት ተጫራቾች
- የዘመኑን ግብር የከፈሉና በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ማቅረብ የሚችሉ
- የአቅራቢነት የምዝገባ ምስክር ወረቀት እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉ።
- ተጫራቾች ተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የተመዝጋቢነት ሰርተፊኬት ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ሰነዱ ላይ የተዘረዘረውን እያንዳንዱን ዋጋ ሞልተው / ፈርመው እና የድርጅቱን ማህተም በማድረግ ፋይናንሻል ኦርጂናል ዶክመንት አንድ እና ፋይናንሽያል ኮፒ አንድ ቴክኒካል ኦርጂናል አንድ እና ቴክኒካል ኮፒ አንድ ለየብቻ በማድረግ በሰም በታሸገ ኤንቬሎፕ አድርገው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ እስከ 15ኛው ቀን 8፡00 ሰዓት ድረስ በድርጅቱ ግዥና ንብረት አስተዳደር አገልግሎት ከፍል በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ ጨረታው ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15ኛው ቀን ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ8፡30 ሰዓት ላይ ይከፈታል፡፡ 15ኛው ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ ጨረታው በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓትና ቦታ ተዘግቶ ይከፈታል።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ (CPO) 50,000 (ሀምሳ ሺህ ብር ብቻ) ቴክኒካል ኦርጂናል ዶክመንት ውስጥ በተረጋገጠ ሲፒኦ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የተዘጋጀውን ዝርዝር የጨረታ ሰነድ በ100.00 ብር ከድርጅቱ ግዥና ንብረት አስተዳደር አገልግሎት ክፍል ቀርበው መግዛት ይችላሉ፡፡
- በጨረታው ሂደት አሸናፊው ድርጅት እቃዎቹን ቢሯችን ድረስ በማምጣት ማስረከብ ይኖርበታል፡፡
- ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር:- 0912818102/0911995805 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡ የድርጅቱ አድራሻ ሆሳዕና ከተማ ወደ ወልቂጤ መውጫ መንገድ ካቶሊክ ት/ቤት ጎን ላይ ነው፡፡
ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥር ድርጅት
ሆሳዕና ኢትዮጵያ
