የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ ከአገልግሎት ውጪ የሆኑትን የእስፖንጅ ፍራሾች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
የሽያጭ ጨረታ
ማስታወቂያ ቁጥር 01/2017
የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ ከአገልግሎት ውጪ የሆኑትን የእስፖንጅ ፍራሾች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም: በጨረታው ላይ ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች በኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ አዋሽ ቢሾላ ወታደራዊ ሙያ ማሰልጠኛ ማዕከል የጨረታውን ሰነድ በመግዛት ጨረታው ላይ መሳተፍ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን ጨረታው ላይ ለመወዳደር የምትፈልጉ፡-
- የጨረታ ሰነድ የተዘጋጀው በኦሮሚኛ ቋንቋ ስለሆነ ተጫራቾች የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ) በመክፈል ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ የስራ ቀናት ከሰኞ እስከ አርብ ለተከታታይ 10 (አስር) ቀናት የጨረታ ሰነዱን በአዋሽ ቢሾላ ወታደራዊ ሙያ ማሰልጠኛ ማዕከል ቅጥር ጊዜ የፋይናንስ ቢሮ በማቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ማንኛውም ተጫራች ጠቅላላ ዋጋ ለውድድር ያቀረቡትን 10% የጨረታ ዋስትና በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ከጨረታ ሰነድ ጋር በፖስታ አሽጎ ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የሚሸጡ የእስፖንጅ ፍራሾች አስመልክቶ ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ሁሌም የስራ ቀናት ከጠዋት ከ3፡00 ጀምሮ እስከ 10፡30 በአካል በመቅረብ ማየት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ዋናውንና ኮፒውን በተናጥል በፖስታ አሽገው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የጨረታው ሰነድ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ የስራ ቀናት ለ10 (አስር) ተከታታይ ቀናት አየር ላይ ቆይተው በ11ኛው ቀን ጠዋት እስከ 4፡00 ሰዓት ተሸጦ የጨረታው ሰነድ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ገብቶ በዚሁ ዕለት ጠዋት 4፡30 ሰዓት ላይ ታሽጎ በ4፡45 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኘበት በይፋ በኮሌጁ አዳራሽ ውስጥ ይከፈታል፡፡
- ኮሌጁ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- አጠቃላይ ዝርዝር መግለጫ ከጨረታ ሰነድ ማግኘት ይችላሉ።
ለበለጠ መረጃ በስ/ቁጥር 09 11 03 37 53 እና 09 73 75 23 04
የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ
