የኤጄሬ ማረሚያ ቤት ከሐምሌ 01/2017 እስከ ታህሳስ 30/2018 ድረስ ለ6 ወር የሚቆይ በስሩ ለሚያስተዳድራቸው ለህግ ታራሚዎች ምግብ አገልግሎት የሚውሉ ነገሮችን በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 1
የኤጄሬ ማረሚያ ቤት ከሐምሌ 01/2017 እስከ ታህሳስ 30/2018 ድረስ ለ6 ወር የሚቆይ በስሩ ለሚያስተዳድራቸው ለህግ ታራሚዎች ምግብ አገልግሎት የሚውል
- የበሰለ ምግብ እና ያልበሰሉ እህሎች፣
- የማገዶ እንጨት፣
- የማጣፈጫ፣
- ሸቀጣሸቀጥ ለሚያቀርቡ በጥቃቅንና አነስተኛ ለተደራጁ ማህበራትም ሆነ ድርጅት እንዲሁም
- ለህግ ታራሚዎች ምግብ ማብሰያ የማገዶ እንጨት፣
- የማጣፈጫ ሸቀጣ ሸቀጥ በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
ስለዚህ በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ማህበራትም ሆኑ ግለሰብ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መመሪያ ማሟላት አለባቸው።
- በንግድ ዘርፍ በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፍቃድ የአቅራቢዎች ምዝገባ የምስክር ወረቀት ወቅታዊ የግብር ግዴታቸውን የተወጡ ለመሆኑ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለበት፡፡ የግብር ከፋይነት (TN NO) ማቅረብ የሚችሉ።
- ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ ወይም የቫት ከፋይነት እንድሁም የምዝገባ ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለበት።
- የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100 (መቶ ብር) በመክፈል ይህ ማስታወቂያ ከወጣ ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት ከወረዳው ማረሚያ ቤት መግዛት ይችላሉ።
- ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ የስራ ቀናት አየር ላይ ውሎ በ16ኛው ቀን ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ከረፋዱ 4፡30 ላይ ተወዳዳሪዎች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው የህግ ታራሚዎች ኮሚቴ የማረሚያ ቤቱ የጨረታ ኮሚቴ እና ከወረዳው አቃቢ ህግ ቢሮ እንዲሁም ከወረዳው ገ/ኢ/ትብብር በሚወከሉ በተገኙበት ጨረታው ይከፈታል። ነገር ግን ጫረታው የሚከፈትበት ቀን መስሪያ ቤቱ ዝግ ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ይሆናል።
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ ምዕ/ሸ/ዞን/ ኤጄሪ ማረሚያ ቤት
ፋይናንስ ክፍል
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር 011-28-30-50-7
የኤጄሬ ወረዳ ማረሚያ ቤት
