የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ዋና መስሪያ ቤት የሚገኘውን የሠራተኛ መዝናኛ ክበብ በውስጡ የሚገኙ የመስሪያ ቁሳቁሶች (ፍሪጅ፣ ማብሰያ ማሽን፣ ወንበር፣ ጠረጴዛ የመሳሰሉትን አካቶ) በኪራይ አገልግሎቱን የሚሰጡ ድርጅቶችን በግልጽ ጨረታ በማወዳደር ለአንድ ዓመት ውል በማስፈረም አገልግሎት ግዥ ለመፈጸም የመንግስትን ግዥ መስፈርቶች ከሚያሟሉ እና በዘርፉ ከተሰማሩ ህጋዊ ድርጅቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
የግዥው መለያ ቁጥር- ኢንሥኮ-ማዕከል ግዥ
ብ/ግ/ጨ/017/2017
የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ዋና መስሪያ ቤት የሚገኘውን የሠራተኛ መዝናኛ ክበብ በውስጡ የሚገኙ የመስሪያ ቁሳቁሶች (ፍሪጅ፣ ማብሰያ ማሽን፣ ወንበር፣ ጠረጴዛ የመሳሰሉትን አካቶ) በኪራይ አገልግሎቱን የሚሰጡ ድርጅቶችን በግልጽ ጨረታ በማወዳደር ለአንድ ዓመት ውል በማስፈረም አገልግሎት ግዥ ለመፈጸም የመንግስትን ግዥ መስፈርቶች ከሚያሟሉ እና በዘርፉ ከተሰማሩ ህጋዊ ድርጅቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
- የሠራተኛ መዝናኛ ክበብ አገልግሎት ግዥ
ስለሆነም በጨረታው ላይ መወዳደር የሚፈልጉ ድርጅቶች ከዚህ በታች የተጠቀሱትን መመዘኛዎች ማሟላት አለባቸው።
- ተጫራቾች የቴክኒክ ሰነዶችን የ2017 የታደስ ንግድ ፈቃድ፣ የግብር ከፋይ ምዝገባ ሰርተፊኬት፣ ወቅታዊ የግብር ክሊራንስ ሰርተፊኬት፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፊኬት ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች ከላይ የተገለጹትን ሰነዶች ከጨረታ ሰነድ ማቅረቢያው ቀነ ገደብ በፊት ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ለሚወዳደሩበት ጨረታ የማይመለስ ብር 400,00 (ብር አራት መቶ) በመክፈል ከሰኔ 5 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ዘወትር ከሰኞ እስከ አርብ ከጠዋቱ 2፡00 6፡30 እንዲሁም ከሰዓት ከ7፡30-11፡00 ሰዓት እንዲሁም ቅዳሜ ከጠዋቱ 2፡30-6፡30 ድረስ ብሎክ 1 ቢሮ ቁጥር 206 ድረስ በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡ (አድራሻው ከስር ተገልጿል።)
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን እስከ ጨረታው መዝጊያ ዕለት እስከ ሰኔ 20 ቀን 2017 ዓም ከጠዋቱ 4፡30 ድረስ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
- ኮርፖሬሽኑ ባዘጋጀው የጨረታ ሰነድ ዋጋ በአቅራቢነት መሞላት ያለበት ተሞልቶ ፊርማና ማህተም ከሌለው ተቀባይነት የለውም፡፡
- ተጫራቾች ከላይ ለተጠቀሰው ጨረታ የጨረታ ማስከበሪያ ብር 10,000 00 (አስር ሺህ ብር) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና በኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ስም አሰርተው ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር ማቅረብ አለባቸው፡፡ ኢንሹራንስ ቦንድና ቼክ ተቀባይነት የላቸውም። የጨረታ ማስከበሪያው ፖስታ ውስጥ ወይም ለብቻው ታሽጎ መቅረብ ይኖርበታል፡፡
- የሻይ ማፍያ ማሽንና ሌሎች ማብሰያዎች ለካፌው የሚያስፈልጉ ዕቃዎች ካሉ ከተጫራቹ ይሆናል፡፡
- ጨረታው ሰኔ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡30 ላይ ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በዋናው መስሪያ ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል።
- አሸናፊው ድርጅት የሰራተኛ መዝናኛ ከበብ አገልግሎት ግዥ ብር 50,000.00 (ሃምሳ ሺህ ብር) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና በኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ስም አሰርተው ውሉን የሚፈጽሙ ይሆናል።
- ኮርፖሬሽኑ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለማንኛውም ማብራሪያ በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ በመደወል መጠየቅ ይቻላል፡፡
በኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን
የግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር
ደብረዘይት መንገድ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጠመንጃ ያዥ ቅርንጫፍ ፊት ለፊት
ስልክ ቁጥር 011 416 73 45/ 011 466 9336
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን
