በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን የጊዶሌ ማረሚያ ተቋም ለ2018 በጀት ዓመት በተቋሙ ሥር ለሚገኙ የሕግ ታራሚዎች የምግብ እህል የምግብ ማጣፈጫ እና ማገዶ እንጨት ከሐምሌ 01 ቀን 2017 እስከ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ከዚህ በታች ያሉ መስፈርቶችን ከሚያሟሉ ድርጅቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን የጊዶሌ ማረሚያ ተቋም ለ2018 በጀት ዓመት በተቋሙ ሥር ለሚገኙ የሕግ ታራሚዎች የምግብ እህል የምግብ ማጣፈጫ እና ማገዶ እንጨት ከሐምሌ 01 ቀን 2017 እስከ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ከዚህ በታች ያሉ መስፈርቶችን ከሚያሟሉ ድርጅቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ስለዚህ ተጫራቾች ማሟላት የሚገባቸው
- በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው
- በዘርፉ የአቅራቢነት ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ
- የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ያላቸው
- የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር /TIN-NO/ ያላቸው
- ቫት ተመዝጋቢ የሆኑ
- የጨረታ ማስከበሪያ ለምግብ እህል ብር 30,000 /ሰላሳ ሺህ ብር/ ለሌሎች ለእያንዳንዳቸው ብር 5,000 /አምስት ሺህ ብር/ በመረጡት ዘዴ ማለትም በባንክ በተመሰከረ CPO ፤ በጥሬ ገንዘብ ወይም የባንክ ዋስትና ማቅረብ ይችላሉ።
- የጨረታ ሰነዱን ጊዶሌ ማረሚያ ተቋም ቢሮ ቁጥር 2 ድረስ በመቅረብ የማይመለስ 100 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል መግዛት ይችላሉ።
- የገዙትንም ሰነድ ኦርጅናልና ኮፒ በማዘጋጀት በሁለት በተለያየ ፖስታ በማሸግ ኦርጅናሉ ላይ ኦርጅናል ኮፒው ላይ ኮፒ ብሎ በመጻፍ ፊርማና ማህተም በማድረግ በ15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ተቋሙ ባዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ።
- የጨረታ ሣጥኑ በ16ኛው ቀን 4፡00 ታሽጎ በዕለቱ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት 4፡30 ላይ የሚከፈት ይሆናል።
- 16ኛው ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ ወደ ቀጣዩ የሥራ ቀን ይተላለፋል።
- ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው አለመገኘት የጨረታ ሂደቱን አያስተጓጉልም።
- የጨረታው አሸናፊ ተለይቶ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ባሉት 7 ተከታታይ የሥራ ቀናት በኋላ አሸናፊው የጠቅላላ ዋጋውን 10% የውል ማስከበሪያ በማስያዝ ውል መግባትና በገባው ውል መሠረት ዕቃዎችን እስከ ተቋሙ ንብረት ክፍል ድረስ የማድረስ ግዴታ አለበት።
- ተቋሙ በጨረታው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0467740595/360/021/359 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን የጊዶሌ ማረሚያ ተቋም
