በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጉምሩክ ኮሚሽን የጋላፊ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት ልዩ ልዩ እቃዎች፣ ስፔርፓርት እቃዎች፣ ኤሌክትሮኒክስ እቃዎች እና ኮስሞቲክስ ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ እንዲሁም ስፔርፓርት እና ኤሌክትሮኒክስ እቃዎች በሀራጅ ጨረታ ሽያጭ ማስታወቂያ ጨ.ቁ 53/2017 ዓ.ም እቃዎቹን ባሉበት ሁኔታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጉምሩክ ኮሚሽን የጋላፊ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት ልዩ ልዩ እቃዎች፣ ስፔርፓርት እቃዎች፣ ኤሌክትሮኒክስ እቃዎች እና ኮስሞቲክስ ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ እንዲሁም ስፔርፓርት እና ኤሌክትሮኒክስ እቃዎች በሀራጅ ጨረታ ሽያጭ ማስታወቂያ ጨ.ቁ 53/2017 ዓ.ም እቃዎቹን ባሉበት ሁኔታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም፡-
- በጨረታው ሽያጭ ስርዓት ለመወዳደር የሚፈልግ ተጫራች በዘርፉ የጸና የታደሰ ንግድ ፍቃድ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፍኬት፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና የዘመኑን ግብር የከፈለ ስለመሆኑ ከግብር ሰብሳቢ መስሪያ ቤት የተሰጠ ማስረጃ ማቅረብ ያለበት ሲሆን በግልጽ ጨረታ ለሚወዳደሩባቸው እቃዎች ከላይ የተጠየቁትን መረጃዎች ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዞ በኤንቨሎፕ በማሸግ ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ሲኖርባቸው ለሀራጅ ጨረታ በጨረታ መክፈቻ ቀን ይዘው መቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ዘወትር በስራ ሰዓት ከሰኞ እስከ አርብ እና ቅዳሜ ጠዋት ከ2፡00-6፡00 ሰዓት ከሰዓት በኋላ ከ9፡00-12፡00 ሰዓት የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በመገኘት፤ ይህ ጨረታ ጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በውርስ መጋዘን አስተዳደር የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 08 በመምጣት መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ለግልጽ ጨረታ ለሚወዳደሩባቸው ዕቃዎች ለምድቡ የሰጡትን ዋጋ አምስት በመቶ (5%) እንዲሁም በሀራጅ ጨረታ ለወጡት ዕቃዎች ለእያንዳንዳቸው 100,000 (አንድ መቶ ሺ ብር) ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (CPO) በጋላፊ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት ስም በባንክ አሰርተው ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች በሚከተለው የጨረታ የጊዜ ሰሌዳ (ስኬጁል) መሠረት መጫረት ይችላሉ፡፡
|
ተ.ቁ |
የቅ/ጽ/ቤቱ ስም |
የጨረታው አይነት |
የንብረት መመልከቻ ቀን የጨረታው ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ |
የጨረታው መዝጊያ እና መክፈቻ ቀንና ሰዓት |
|
1 |
ጋላፊ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት |
ግልጽ ጨረታ |
እስከ 11/10/2017 |
11/10/2017 ዓ.ም 3፡30 ሰዓት ተዘግቶ ወዲያውኑ ይከፈታል። |
|
2 |
ጋላፊ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት |
ሐራጅ ጨረታ |
እስከ 11/10/2017 |
11/10/2017 ዓ.ም ግልጽ ጨረታ እንደተጠናቀቀ ሐራጅ ጨረታ ይጀምራል። |
- የጨረታው መክፈቻ ቦታ፦ በጋላፊ ጉ/ቅ/ጽ/ቤት የሚካሄድ ሲሆን ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በሚገኙበት ይከፈታል፡፡ ተጫራቾች በተራ ቁጥር አንድ የተጠቀሱ ማስረጃዎች ኦርጅናል ይዘዉ መቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች ያስያዙትን ዋስትና (CPO) በተመለከተ ለአሸናፊው ተጫራች ካሸነፉት የዕቃ ዋጋ ላይ የሚታሰብላቸው ሲሆን ለተሸናፊ ተጫራቾች የጨረታ ውጤቱ በተገለጸ በ3 (ሶስት) ቀናት ውስጥ ተመላሽ ይደረግላቸዋል፡፡
- አሸናፊ ተጫራች ማሸነፋቸውን በደብዳቤ ከተገለጸላቸው ቀን ጀምሮ በ05 (በአምስት) ቀናት ውስጥ ያሸነፉበትን እቃ ዋጋ ገቢ በማድረግ እቃውን መረከብ ያለበት ሲሆን ይህን ባይፈጽም ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ዋስትና ለመስሪያ ቤቱ ገቢ ተደርጎ ዕቃው በድጋሜ ለጨረታ የሚቀርብ ሲሆን ነገር ግን የእቃውን ዋጋ ገቢ አድርጎ በተቀመጠው ጊዜ ውስጥ እቃውን ያላነሳ እንደሆነ ለሚቆይበት ተጨማሪ ጊዜ የመጋዘን ኪራይ የሚከፍል ይሆናል፡፡ ሆኖም እቃውን በሁለት ወር ውስጥ ካላወጣ ለንብረቱ የተከፈለው ዋጋ ለመስሪያ ቤቱ ገቢ ሆኖ እቃው እንደተተወ ተቆጥሮ በሽያጭ ይወገዳል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ በስ/ቁ፡- 0335590114 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የጋላፊ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት
