የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሴቶች፣ ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ በ2018 በጀት አመት በስሩ ለሚገኙ ተቋማት ተገልጋዮችና ከጎዳና ለሚነሱ ዜጎች አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ ግዥዎችን በግልፅ ጨረታ ተጫራቾችን አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የግዥ ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር አ/አ/ከ/አ/ሴ/ህ/ማ/ጉ/ቢሮ (06/001-004/2017)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሴቶች፣ ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ በ2018 በጀት አመት በስሩ ለሚገኙ ተቋማት ተገልጋዮችና ከጎዳና ለሚነሱ ዜጎች አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ ግዥዎችን በግልፅ ጨረታ ተጫራቾችን አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
|
ሎት ቁጥር |
የሚገዛው እቃ/አገልግሎት |
የጨረታ ማስከበሪያ መጠን |
|
ሎት 1 |
የተለያዩ የምግብ ግብዓቶች ግዢ |
100,000.00 CPO |
|
ሎት 2 |
የተለያዩ የፅዳት እቃዎች ግዢ |
100,000.00 CPO |
|
ሎት 3 |
የበሰሉ ምግቦች አቅርቦት ግዢ |
100,000.00 CPO |
|
ሎት 4 |
የህዝብና የጭነት መኪና አገልግሎት ግዢ |
50,000.00 CPO |
ስለዚህ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የግዥና የፋይናንስ መመሪያዎች የምታሟሉ ተጫራቾች በጨረታው መሳተፍ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
- በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉበትን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
- በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ መኖራቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ።
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /TIN/ ያላቸውና ማቅረብ የሚችሉ።
- የተጨማሪ እሴት ታክስ /VAT/ ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር የያዘ የጨረታ ሰነድ ለእያንዳንዱ ሎት የማይመለስ ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ በቢሮ አካውንት 1000009650559 በማስገባት ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 10 የስራ ቀናት እስከ 11ኛው ቀን 4፡00 ሰዓት ድረስ ከቢሮው ክፍያና ሂሳብ ዳይሬክቶሬት ደረሰኝ በማስቆረጥ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ በገዙት የጨረታ ሰነድ ላይ በስፔስፊኬሽኑ መሰረት ብቻ ሞልተው እና በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ላይ ኮፒና ዋና (ኦርጅናል) ሰነድ ብለው በ2 ፖስታ በመለየት የግዥ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት እለት ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 10 የስራ ቀናት እስከ 11ኛው ቀን 4፡00 ሰዓት ድረስ ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው። ጨረታው ከላይ በተገለፀው ቀንና ሰዓት ታሽጐ በእለቱ 4፡30 ሰዓት በቢሮው መሰብሰቢያ አዳራሽ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች ሌሎች መረጃዎችን ከጨረታ ሰነዱ ላይ ማግኘት የሚችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
- ቢሮው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- የጨረታ ማስከበሪያ በCPO ነው።
- ተጫራቾች ናሙና ለሚጠየቅባቸው እቃዎች ናሙና ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
ማሳሰቢያ፡- የጨረታ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 11ኛው የስራ ቀን 4፡00 ሰዓት ላይ ታሽጎ 4፡30 ሰዓት ጨረታው ይከፈታል፡፡
አድራሻ፡- አ/አ/ከ/ሴ/ህ/ማ/ጉ/ቢሮ ደጃች ውቤ ከጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ወደ አፍንጮ በር አደባባይ በሚወስደው መንገድ የስድስት ኪሎ/የፈረንሳይ ታክሲ መጫኛ አለፍ ብሎ ቢሮ ቁጥር 206 1888 ህንፃ ላይ 2ኛ ፎቅ ስልክ ቁጥር 09 47 95 17 60/09 42 12 94 92
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሴቶች፤ ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ
