የጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ ሎት 1 የተማሪ ወንበር እና ጠረጴዛ ጥገና የእጅ ዋጋ 1 ሎት 2 የወንበር እና የጠረጴዛ መስሪያ ማቴርያል እቃ አቅርቦት ግዥ፣ ሎት3 የተማሪዎች የእጅ መታጠቢያ ስራ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛትና ማሰራት ይፈልጋል፡፡
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር ጎመትኮ ግ/ፋ/ን/ አስ -2 /718/17
የጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ ሎት 1 የተማሪ ወንበር እና ጠረጴዛ ጥገና የእጅ ዋጋ 1 ሎት 2 የወንበር እና የጠረጴዛ መስሪያ ማቴርያል እቃ አቅርቦት ግዥ፣ ሎት3 የተማሪዎች የእጅ መታጠቢያ ስራ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛትና ማሰራት ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ይጋብዛል፡፡
- በዘመኑ የታደሰ የሚመለከተው ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው።
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን ነምበር) ያላቸው።
- የግዥው የብር መጠን 200,000.00 /ሁለት መቶ ሺ ብር/ እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆን አለበት ለዚህም ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል፡፡
- ተጫራቾች ከነ - 3 የተዘረዘሩትን ማስረጃዎች ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ከዚህ በፊት በተሰጣቸው የእቃ አቅርቦት ወይም አገልግሎቶች ችግር ኖሮባቸው በየደረጃው በተቀመጠው አግባብ ባለውና በሚመለከተው አካል እርምጃ ያልተወሰደባቸው መሆን አለባቸው፡፡
- የሚሰሩ ስራዎችን አይነትና መግለጫ ከመጫረቻ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡ ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ 100 ብር በመክፈል ሎት 1 እና 2 ከ06/10/2017 ዓ/ም እስከ 25 /10/2017 ዓ.ም ፤ ሎት3 ከ06/10/2017 ዓ/ም እስከ 2/11/2017 ዓ.ም ዘወትር በስራ ሰዓት ቢሮ ቁጥር 5 ወይም 19 መግዛት እና ማስገባት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የሞሉትን ጠ/ዋጋ 1% በባንክ በተረጋገጠ ሲፒአ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ በአማርኛ የተተረጎመ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማቅረብ አለበት። በጥሬ ገንዘብ የሚያስይዙ ከሆነ በውስጥ ገቢ ደረሰኝ መቁረጥ አለበት ፡፡
- ማንኛውም ተጫራች ሰነዱን በአንድ ወጥ በጥንቃቄ በታሸገ ኤንቨሎፕ ፖስታ በጎንደር መም/ኮሌጅ በግ/ፋ/ን/አስ የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 2 ዘወትር በስራ ሰአት ሎት1 እና ሎት2 በ26/10/17 ዓ.ም 3፡30 ሰዓት ታሽጎ 4፡00 ይከፈታል፡፡ ሎት3 በ3/11/2017 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጎ/መ/ት/ኮ ቢሮ ቁጥር G-01 በ3፡30 ታሽጎ በ4፡00 ሰአት ይከፈታል ፡፡ ነገር ግን ቀኑ በዓል ከሆነ የሚቀጥለው ቀን ይከፈታል፡፡
- ኮሌጁ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ኮሌጁ ቫት ሰብሳቢ በመሆኑ የቫት ሂሳብን 7.5% ቆርጠን የምናስቀር መሆኑን እንገልጻለን፡፡
- ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገ ጎ/መ/ት/ኮሌጅ በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 0581121634 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ
